“እግዚአብሔር ኃያል ነኝ ሲል እሳትን ፈጠረ“ (መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት)
ታላቁ የቤተ ክርስቲያናችን አባት ሊቀ መዘምራን ዕቁበ ጊዮርጊስ ሲናገሩ “እግዚአብሔር ኃያል ነኝ ሲል እሳትን ፈጠረ“ ይላሉ፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 807 entries already.
ታላቁ የቤተ ክርስቲያናችን አባት ሊቀ መዘምራን ዕቁበ ጊዮርጊስ ሲናገሩ “እግዚአብሔር ኃያል ነኝ ሲል እሳትን ፈጠረ“ ይላሉ፡፡
እግዚአብሔር በዕለተ ሰኑይ በቀዳሚት ሰዓት ሌሊት ‹‹ጠፈር ይሁን፤ ውኃም ከውኃ ይለይ›› ብሎ ቢያዘው ከዚህ እስከ ብሩህ ሰማይ ሞልቶ የነበረውን ውኃ ከአራት ከፍሎ አንድን እጅ በመካከል ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ ዘረጋው፡፡ (ዘፍ.፩፥፮) እንደ ቤተ መንግሥት አዳራሽ ወደ ላይ ጠበብ አድርጎ እንደ ብረት አጸናው፤ ይህ የምናየው ሰማይ ነው፤ ጠፈር ይባላል፡፡ ጠፈር ማለትም ሥዕለ ማይ (የውኃ ሥዕል) ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ጠፈርን መፍጠሩ ስለምንድነው? ቢሉ ረቡዕ የሚፈጥረውን ፀሐይን ሊያቀዘቅዝ ሰውም ይህን እያየ ሰማያዊ ርስት እንዳለው እንዲያውቅ ነው፡፡ እጅግም ነጭ ከሆነ ዓይን እየበዘበዘ እያንጸባረቀ ለሰው የደዌ ምክንያት ይሆን ነበርና፡፡ በድስት ያለ ውኃ በሚታጠብ ጊዜ የእሳት ማቃጠል ሲበዛበት እንደሚሰበር ጠፈርም የፀሐይ ማቃጠል ሲበዛበት እንደ ሸክላው በፈረሰ ነበርና እንዲያጸናው ሐኖስን በላይ አደረገለት፡፡ (መጸሐፈ ሥነ ፍጥረት ገጽ ፳-፳፫
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? መምህራን የሚነግሯችሁን በትኩረት በማዳመጥ፣ መጻሕፍትን በማንበብና ያልገባችሁን በመጠየቅ ትላንት ከነበራችሁ ግንዛቤ የተሻለ ዕውቀትን እየቀሰማችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! መልካም!
ውድ የእግአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት በዓላትን አስመልክተን የቅዱሳንን ታሪክ አዘጋጅተን ባቀረብንላችሁ መሠረት ከቅዱሳን የሕይወት ታሪክ በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? በተለይ ሥርዓትን አክብረን መኖረ እንደሚገባን፣ በቤተ እግዚአብሔር መኖር ደግሞ ታላቅ በረከትን እንደሚያስገኝልን፣ ለቅዱሳን ስለተሰጣቸው ክብርና የቅድስና ሕይወታቸው ምን እንደሚመስል ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ያዘጋጀንላችሁ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ትምህርት ሲሆን ሐሰት መናገር እንደማይገባ እንዲሁም እውነተኛና ታማኝ መሆን እንዳለብን ልናስተምራችሁ ወደድን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የጥቅምት ወር የመጨረሻ ክፍለ ጊዜያችን የሆነውን ትምህርት ለዛሬ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ከዚያ በፊት ግን የባለፈው ትምህርታችን ላይ ስላስተማርናችሁ ‹‹ረብሐ ግሥ›› ጥቂት እናስታውሳችሁ፡፡
ከግሥ ዓይነቶች አንዱ የሆነው ረብሐ ግሥ ዘማች ግሦችን ከቀዳማይ አንቀጽ ጀምሮ እስከ አርእስት እና ከዚያ በላይ ያሉትን ቅጽሎችን የሚያገሰግስ ማለት እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ በዚህ የግሥ ዓይነት ሥር የሚገኙት የዋህና መሠሪ ግሦች መሆናቸውንና እነርሱንም በግሥ አርእስት ማለትም በቀተለ፣ በቀደሰ፣ በተንበለ፣ በባረከ፣ በማህረከ፣ በሴሰየ፣ በክህለ እና በጦመረ ዘርዝረን ለማየት ሞክረናል፡፡ የዚህንም ግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳጠናችሁት ተስፋ እያደረግን ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናልፋለን፡፡ ከዚህ ቀጥሎ የምንመለከተው የግሥ ዓይነት ‹‹ሥረይ ግሥ›› ይባላል፡፡
ሊሄድ በ’ኔ መንገድ
ሊከተለኝ ‘ሚወድ
ራሱን ለሚክድ
አይደንግጥ አይፍራ
አለሁ ከር’ሱ ጋራ
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምድር በገነት ወይም በሲኦል ልትመሰል እንደምትችል ያስረዳሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ወርቃማ ዘመናት ተብሎ የሚጠሩትንም በመጥቀስ የተመረጡ ቅዱሳን ነገሥታት የነገሡበት፣ ደጋግ አባቶች የኖሩበት፣ ሊቀ ጳጳሳትና ጳጳሳት እንዲሁም ቀሳውስትና ካህናት በበጎና በመልካም መንገድ ምእመናንን መርተው በቅድስና ሕይወት ለርስተ መንግሥተ ሰማያት ባበቁበት ጊዜ ምድር በገነት ትመሰል እንደነበር ያስረዳሉ፡፡
በሀገረ አንጾኪያ ከአሕዛብ ወገን የተለወደው አይሁዳዊው ሉቃስ ከሰባ ሁለቱ አርድእት የተቆጠረ ባለ መድኃኒትና ወንጌልን የጻፈ ቅዱስ ሐዋርያ ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ትርጓሜያቸው ስሙ ‹ዓቃቤ ሥራይ› ወይም ‹ባለ መድኃኒት› የሚል ትርጉም በውስጡ የያዘ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ በላቲን ቋንቋ ‹ሉካስ› ማለት ‹ብርሃናማ፣ ብርሃን የያዘ› ማለት ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ ብልህና ጥበበኛ በማለት ይገልጸዋል፡፡
በዐሥራ ስምንት ዓመት ዕድሜው የመነኮሰ፣ ትዕግሥቱ እጅግ የበዛ እንዲሁም የመታዘዝ ጸጋ የተሰጠው ቅዱስ አባታችን ዮሐንስ ሐጺር የዕረፍት መታሰቢያ ጥቅምት ሃያ ቀን ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚገልጹትም ይህ ጻድቅ ከቅዱሳን አባቶች መካከል በቁመት እንደ እርሱ አጭር ስላልነበረ ‹‹ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር፤ አጭሩ አባ ዮሐንስ›› ተብሏል፡፡ የእርሱን ቁመትና የቅድስና ሕይወቱን ሲያነጻጽሩም ‹‹ቁመቱ እጅግ ያጠረ ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን›› በማለት ተናግረዋል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም በክረምቱ የዕረፍት ጊዜያችሁ ትምህርት እስኪከፈት በጣም ጓጉታችሁ እንደነበር እናስባለን! ይኸው ተከፈተላችሁ! እንግዲህ በርትታችሁ ከአሁኑ መማር፣ ማጥናት፣ የቤት ሥራን መሥራት፣ ያልገባችሁን መጠየቅ ይገባችኋል፡፡ ገና ነው እያላችሁ እንዳትዘናጉ ጥናቱን አሁኑኑ ጀምሩ! የጨዋታም ሆነ ቴሌቪዥን የምታዩበት ጊዜ ከትምህርታችሁ ጋር በማይጋጭ መልኩ መሆን አለበት፡፡ ከሁሉም ትምህርታችሁን አስቀድሙ! ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሊቀ ዲያቆናትና የቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ታሪክ ነው፡፡
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የጥቅምት ወር የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜያችን ወደ ሆነው ትምህርት ከመግባታችን በፊት ስለ ባለፈው ጥቂት እናስታውሳችሁ፡፡ ከዘመን መለወጫ ጋር ተያይዞ ለንግግር የሚጠቅሙንን የመግባቢያ ዓረፍተ ነገሮችና የንግግር ስልቶች አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ ይህም ለእናንተ የንግግር ክህሎት በሚረዳ መልኩ አዘጋጅተን ያቀረብንላችሁ በ፳፻፲፬ ዓመተ ምሕረት በድረ ገጹ በቀረቡት ትምህርቶች የተማራችኋቸውን ቃላትም ሆነ ግሦች በመጠቀም እንድትለማመዷቸው በማሰብ ነው፤ ይህንን ተግባራዊ እንዳደረጋችሁትም ተስፋችን ነው፡፡
ታስታውሱ እንደሆነ ያለፈው ዓመት የመጨረሻ ትምህርታችን ስለ ነገረ ግሥና አገባብ ነበር፤ እንደሚታወቀው ዓረፍተ ነገሮችን ለመሥራት የሚጠቅሙን ከስሞች ቀጥሎ በዋነኛነት ግሦች በመሆናቸው በእነርሱ ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገን በዚህ ሳምንት ያቀረብንላችሁ ትምህርት ከግሥ ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው ‹ረብሐ› ግሥ ነው፡፡