ከውድቀት አነሣን!
ለሰሚው በሚከብድ ቃላት በማይገልጸው
በመከራ ውሎ አዳምን አዳነው!
ዲያብሎስ ታሠረ አዳም ነጻ ወጥቶ
ልጅ ተባለ ዳግም በደሉ ተረስቶ
የማይሞተው አምላክ ስለ እኛ ሲል ሞቶ
ከውድቀት አነሣን ልጅነትን ሰጥቶ!
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1023 entries already.
ለሰሚው በሚከብድ ቃላት በማይገልጸው
በመከራ ውሎ አዳምን አዳነው!
ዲያብሎስ ታሠረ አዳም ነጻ ወጥቶ
ልጅ ተባለ ዳግም በደሉ ተረስቶ
የማይሞተው አምላክ ስለ እኛ ሲል ሞቶ
ከውድቀት አነሣን ልጅነትን ሰጥቶ!
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስት ቁጥር ፻፷፬ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት ፲፩ እስከ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡
እንደዚህ እንደኛ ያለ ክፉ ዘመን የገጠማቸው፣ መጥፎውን ትቶ በጎውን፣ ጠማማውን ሳይሆን ቀናውን፣ የጨለማውን ሳይሆን የብርሃኑን ጎዳና የሚያሳያቸው፣ የሚነግራቸውና የሚያስተምራቸው ያጡ፣ ግራ የተጋቡ ሕዝቦችን የተመለከተበትን ነገር እየነገረን ይመስላል ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው ይህንን ኃይለ ቃል የነገረን፡፡
የምድር መናወጥ ወይም መንቀጥቀጥ በታሪክ መመዝገብ ከተጀመረበት ዘመን አንሥቶ እስከደረስንበት ዘመን ድረስ ከባድ የሚባል በሬክተር ስኬል ሰባት ነጥብ ሁለት እና ከዚያ በላይ በዐሥርት ዓመታት ቢበዛ አንድ ጊዜ ነበር የሚከሠተው፡፡ ከ፲፱፻ ዓ.ም ወዲህ ግን ክብደቱም ብዛቱም የሚያደርሰውም ሰብአዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊና መሠረተ ልማታዊ ውድመቱና ጥፋቱ ጨምሯል፡፡ ከ ፲፱፻ እስከ ፲፱፻፵፱ በየዐሥርት ዓመቱ የሚደርሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ሦስት እና ከዚያ በላይ ሆኗል፡፡ በ፲፱፻፶ዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ ዘጠኝ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ በ፲፱፻፸ዎቹ ፻፳፭ አደገኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ ይህንን ሁኔታ ስንመለከተው ምድራችን በመሬት መንቀጥቀጥ ብዛትና ክብደት እየፈረሰች መሄዷ የማይቀር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
አዳም ያየ መስሎት ዓይኑ እንደተዘጋ
ይኖር ነበር ገነት ብቻውን ሲተጋ
ሔዋን ባትቀጥፈው የበለሱን ፍሬ
መቼ ይሰማ ነበር የአምላክ ልጅ ወሬ
አዳም የተከለው የፍቅር አበባ አድሮ እየጐመራ
አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን አብቦ ቢያፈራ
ከላይ ከሰማያት መንበረ ጸባኦት
የአምላክን አንድ ልጅ መዓዛው ጐትቶት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? በርትታችሁ እየተማራችሁ ነውን? ጥናቱንም ከወዲሁ ጀምሩ! ያልገባችሁንም ጠይቁ! መንፈሳዊ ትምህርትንም በዕረፍት ቀናችሁ ተማሩ፤
ወደፊት ለመሆን የምትፈልጉትን ለመሆን አሁን በርትታችሁ ተማሩ! ቤት ስትገቡ የቤት ሥራችሁን ብቻ ሳይሆን መሥራት ያለባችሁ የተማራችሁትንም መከለስ ነው! ከዚያም ያልተረዳችሁትን መምህራችሁን ጠይቁ፤ መልካም!
ባለፈው ትምህርታችን ጥያቄዎች አቅርበንላችሁ ምላሶቹን ልካችሁልን ነበር፤ እኛም ትክክለኛ የሆኑትን ምላሾች ነግረናቹኋል፤ ለዛሬ ደግሞ “አማላጅነት” በሚል ርእስ እንማራለን! ተከታተሉን!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ
የአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ተጋድሎ በጽኑ መሠረት ላይ በመገንባቱ የመከራ ዝናብ ቢዘንብ፣ የሥቃይ ጎርፍ ቢጎርፍ፣ የችግር ነፋስ ቢነፍስ አይወድቅም፡፡ (ማቴ.፯፥፳፭) ይህም የሆነው እነርሱን በመንፈሳዊ ሕይወት የተተከለ፣ በተጋድሎ ያሳደገ፣ ገቢረ ተአምራት ወመንክራት በማድረግ እንዲያብቡ ያደረገና ለፍሬ ክብር ያበቃ የክብር ባለቤት አምላካችንና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ነው፡፡
በኃጢአት ተፀንሼ በዐመፃ ተወልጄ
ከቃልህ ሕግ ወጥቼ በዝንጉዎች ምክር ሄጄ
በኃጢአተኞች መንገድ ቆሜ በዋዘኞች ወንበር ተቀምጬ
በውኃ ማዕበል ሰጥሜ የሞት ጽዋን ጨልጬ
