Entries by Mahibere Kidusan

‹‹በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ ብዙዎች ናቸው›› (መዝ.፬፥፮)

እንደዚህ እንደኛ ያለ ክፉ ዘመን የገጠማቸው፣ መጥፎውን ትቶ በጎውን፣ ጠማማውን ሳይሆን ቀናውን፣ የጨለማውን ሳይሆን የብርሃኑን ጎዳና የሚያሳያቸው፣ የሚነግራቸውና የሚያስተምራቸው ያጡ፣ ግራ የተጋቡ ሕዝቦችን የተመለከተበትን ነገር እየነገረን ይመስላል ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው ይህንን ኃይለ ቃል የነገረን፡፡

“የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል” (ማቴ.፳፬፥፯)

የምድር መናወጥ ወይም መንቀጥቀጥ በታሪክ መመዝገብ ከተጀመረበት ዘመን አንሥቶ እስከደረስንበት ዘመን ድረስ ከባድ የሚባል በሬክተር ስኬል ሰባት ነጥብ ሁለት እና  ከዚያ በላይ በዐሥርት ዓመታት ቢበዛ አንድ ጊዜ ነበር የሚከሠተው፡፡ ከ፲፱፻ ዓ.ም ወዲህ ግን ክብደቱም ብዛቱም የሚያደርሰውም ሰብአዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊና መሠረተ ልማታዊ ውድመቱና ጥፋቱ ጨምሯል፡፡ ከ ፲፱፻ እስከ ፲፱፻፵፱  በየዐሥርት ዓመቱ የሚደርሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ሦስት እና ከዚያ በላይ ሆኗል፡፡ በ፲፱፻፶ዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ ዘጠኝ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ በ፲፱፻፸ዎቹ ፻፳፭ አደገኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ ይህንን ሁኔታ ስንመለከተው ምድራችን በመሬት መንቀጥቀጥ ብዛትና ክብደት እየፈረሰች መሄዷ የማይቀር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡

የዛፉ ፍሬ

አዳም ያየ መስሎት ዓይኑ እንደተዘጋ
ይኖር ነበር ገነት ብቻውን ሲተጋ

ሔዋን ባትቀጥፈው የበለሱን ፍሬ
መቼ ይሰማ ነበር የአምላክ ልጅ ወሬ

አዳም የተከለው የፍቅር አበባ አድሮ እየጐመራ
አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን አብቦ ቢያፈራ
ከላይ ከሰማያት መንበረ ጸባኦት
የአምላክን አንድ ልጅ መዓዛው ጐትቶት

አማላጅነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? በርትታችሁ እየተማራችሁ ነውን? ጥናቱንም ከወዲሁ ጀምሩ! ያልገባችሁንም ጠይቁ! መንፈሳዊ ትምህርትንም በዕረፍት ቀናችሁ ተማሩ፤

ወደፊት ለመሆን የምትፈልጉትን ለመሆን አሁን በርትታችሁ ተማሩ! ቤት ስትገቡ የቤት ሥራችሁን ብቻ ሳይሆን መሥራት ያለባችሁ የተማራችሁትንም መከለስ ነው! ከዚያም ያልተረዳችሁትን መምህራችሁን ጠይቁ፤ መልካም!

ባለፈው ትምህርታችን ጥያቄዎች አቅርበንላችሁ ምላሶቹን ልካችሁልን ነበር፤ እኛም ትክክለኛ የሆኑትን ምላሾች ነግረናቹኋል፤ ለዛሬ ደግሞ “አማላጅነት” በሚል ርእስ እንማራለን! ተከታተሉን!

የአቋም መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ

የአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ተጋድሎ በጽኑ መሠረት ላይ በመገንባቱ የመከራ ዝናብ ቢዘንብ፣ የሥቃይ ጎርፍ ቢጎርፍ፣ የችግር ነፋስ ቢነፍስ አይወድቅም፡፡ (ማቴ.፯፥፳፭) ይህም የሆነው እነርሱን በመንፈሳዊ ሕይወት የተተከለ፣ በተጋድሎ ያሳደገ፣ ገቢረ ተአምራት ወመንክራት በማድረግ እንዲያብቡ ያደረገና ለፍሬ ክብር ያበቃ የክብር ባለቤት አምላካችንና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ነው፡፡

ወዮልኝ!

በኃጢአት ተፀንሼ በዐመፃ ተወልጄ
ከቃልህ ሕግ ወጥቼ በዝንጉዎች ምክር ሄጄ
በኃጢአተኞች መንገድ ቆሜ በዋዘኞች ወንበር ተቀምጬ
በውኃ ማዕበል ሰጥሜ የሞት ጽዋን ጨልጬ

የተራበችው ነፍሴ!

ቀንና ሌት ዙሪያዬን ከቦ ሲያስጨንቀኝ፣ ሲያሠቃየኝ የኖረው ባዕድ ከእኔ ባልሆነ መንፈስ ሊገዛኝና ከበታቹ ሊያደርገኝ ሲጥር በዘመኔ ኖሯል፡፡ ሥቃይና ውጥረት በተቀላቀለበት መከራ ውስጥ ብኖርም ሁል ጊዜ ተስፋን ማድረግ አላቆምኩም፤ ሆኖም ተፈጥሮዬ የሆነውን ሰላም ስናፍቅ የሰማይን ያህል ራቀብኝ፡፡

ወርኃ ጥቅምት

የጥቅምት ወርን በተመለከተ መጽሐፈ ስንክሳር በወርኃ ጥቅምት ንባብ መግቢያው “የጥቅምት ወር የቀኑ ሰዓት ዐሥራ አንድ ነው፤ ከዚህም በኋላ ይቀንሳል” ይላል፤ ይህም ማለት በቀን ውስጥ ካለው ሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የሌሊቱ ሰዓት ዐሥራ ሦስቱን ሲይዝ የቀኑ ጊዜ ደግሞ ዐሥራ አንዱን ሰዓት ይይዛል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በጥቅምት ወር የሌሊቱ ጊዜ ቀኑ ጊዜ ይረዝማል ማለት ነው፡፡

ጥቅምት ቃሉ “ጠቂም ጠቂሞት” ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም “የተሠራች፣ ሥር” ማለት ነው፤ ዓለም የተፈጠረው በዚህ ወር በመሆኑ “ጥንተ ግብር (የሥራ መጀመሪያ)” ማለት ነው፡

ጥቅምት የሚለውን ቃል ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙ “ስመ ወርኅ፣ ካልእ መስከረም፣ ጽጌውን መደብ አድርጎ ፍሬ፣ ወርኃ ፍሬ፣ መዋዕለ ሰዊት ይሰኛል” ይላሉ፡፡ (መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ፭፻፰)