ማኅቶት!
ለጨለመው ሕይወት ሆኖለት ማኅቶት፣
በብርሃኑ ጸዳል ሰውሮት ከጽልመት ፡፡
የክህነትን ሥልጣን፣ ሥጋውና ደሙን ፣ የንስሐን መንገድ፣
በፍቅሩ ለግሶ መዳንን ለሚወድ፡፡
ያናገረው ትንቢት የሰጠው ምሳሌ፣ በአማን ተፈጽሞ፣
በይባቤ መልአክ በዕልልታው ደግሞ፣
እያለ ከፍ ከፍ ረቆ ያይደለ! እያዩት በርቀት፣
ዐረገ ወደ ላይ ወደ ክቡር መንበሩ ሰማየ ሰማያት፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 975 entries already.
ለጨለመው ሕይወት ሆኖለት ማኅቶት፣
በብርሃኑ ጸዳል ሰውሮት ከጽልመት ፡፡
የክህነትን ሥልጣን፣ ሥጋውና ደሙን ፣ የንስሐን መንገድ፣
በፍቅሩ ለግሶ መዳንን ለሚወድ፡፡
ያናገረው ትንቢት የሰጠው ምሳሌ፣ በአማን ተፈጽሞ፣
በይባቤ መልአክ በዕልልታው ደግሞ፣
እያለ ከፍ ከፍ ረቆ ያይደለ! እያዩት በርቀት፣
ዐረገ ወደ ላይ ወደ ክቡር መንበሩ ሰማየ ሰማያት፡፡
ተወዳጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ በሰላም አደረሳችሁ! በክፍል ስድስት ክብረ ምንኩስና ትናንት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የነበረውን ክብርና ሞገስ ያስገኘውን የቅድስና ፍሬና ያሳረፈውን አሻራ፣ በክፍል ሰባት ደግሞ ምንኩስና ዛሬ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እያጋጠመው ያለውን ተግዳሮት አንሥተን የተወሰኑ ችግሮችን ለማቅረብ ሞክረን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ክፍል ስምንትን አቅርበንላችኋልና ተከታተሉን!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዓለ ሃምሳ ተብሎ የሚታወቀውን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? መቼም ልጆች! ጾም የለም ብላችሁ ጸሎት ተግቶ ከመጸለይ፣ ቤተ ክርስተያን በሰንበት በዕረፍት ጊዜያችሁ ሄዶ ማስቀደስን እንደማትዘነጉ ተስፋ እናደርጋለን!
በዘመናዊ ትምህርታችሁም ሁለተኛው የመንፈቀ ዓመት እየተገባደደ በመሆኑ ለማጠቃለያ ፈተና የምትዘጋጁበት ወቅት በመሆኑ በርትታችሁ አጥኑ፤ መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ! ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ‹‹ምሥጢረ ጥምቀትን›› ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ምሥጢረ ጥምቀትን ቀጣይ ክፍለ ትምህርት እንማራለን፤ ተከታተሉን!
ወዳጄ ሆይ! የምትጓዝበትን መንገድ የማታውቅ ከሆነ ትጠፋለህና በየትኛው መንገድ ላይ ልትራመድ እንደሚገባህ ልታገናዝብ ያስፈልግሃል። በፊትህ ሰፊ፣ አታላይና ጠባብ መንገዶች አሉና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ በማለት አስጠንቅቋቸዋል። ‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና፤…፡፡›› (ማቴ.፯፥፲፫)
ዘለዓለማዊ ሕይወትን የማገኝብሽ ባለ መልካሟ መዓዛ ፍሬ የአምላኬ ስጦታ ነሽ፤ በገነት ፈጥሮ ቢያሳየኝ ሳላውቅሽ መቅረቴና ልመገብሽ ባለመቻሌ እጅጉን ኀዘን ይሰማኝ ነበር፡፡ ፈጣሪ በአንቺ ሕይወትን ሊሰጠኝ ጣፋጭ አድርጎ ቢፈጥርሽ ሳላውቅሽ ያልታዘዝኩትን ፍሬ በልቼ መራራ ሞትን በራሴ አመጣሁ፡፡ አሁን ግን አወኩሽ! የሕይወቴ ጣፋጯ ፍሬ በአንቺ ነፍሴ ተፈውሳለችና፡፡
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!
ከመቅረዜ ላይ አድርጌ ለኮስኳት፡፡ እርሷም ቦገግ ብላ አበራችልኝ፡፡ ከመብራቷ የሚወጣውን ብርሃን ስመለከት ውስጤ ሰላም ይሰማኛል፤ ተስፋም አገኛለሁ፤ በጨለማ ውስጥ መብራት ብርሃን እንደሚሰጥ ሁሉ በጭንቅ፣ በመረበሽ እና በሁከት ተወጥሮ ለሚጨነቅ አእምሮዬ ወገግ ብላ እንደምታበራ ብርሃኔ ሆነችኝ፡፡…
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ‹‹በዓለ ደብረ ምጥማቅ›› አደረሳችሁ!
አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለ መታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁላችንም ታላቅ በዓልን እናደርጋለን።