33 2007 3

33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የሦስተኛ ቀን ውሎ

ጥቅምት 7 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

የ33ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሀገረ ስብከቶችን የ2006 ዓ.ም. የሥራ ክንውን ሪፖርት አደመጠ፡፡

33 2007 3ሦስተኛ ቀኑን የያዘው ይህ ጉባኤ በሀገረ ስብከቶች አማካኝነት የቀረበውን ሪፖርቶች ያደመጠ ሲሆን በአብዛኛው የሀገረ ስብከቶች ሪፖርት ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን የሚያደርገውን ሁለገብ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን በሪፖርቶቹ የቀረቡ ሲሆን የጉባኤው ታዳሚም አድናቆቱን በጭብጨባ ገልጿል፡፡

በመርሐ ግብሩ መሠረት በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት ሊደረግ የነበረ ቢሆንም በጊዜ መጣበብ ምክንያት በተያዘው መርሐ ግብር ያልተካሔደ ሲሆን በጉባኤው ማጠቃለያ ዕለት ነገ ጥቅምት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ውይይቱ ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

33 2nd 2 1

33ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው እንደቀጠለ ነው፡፡

ጥቅምት 6 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 5 ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም የተጀመረው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ቀጥሏል፡፡ በጥቅምት 5 ቀን የከሰዓት ውሎና ጥቅምት 6 ቀን ጠዋት 24 አህጉረ ስብከቶች ሪፓርቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡

ከቀረቡት ሪፓርቶች በዋናነት ትኩረት የሳቡት

  • ለልማት ሥራ ትኩረት መሰጠቱ

  • አዳዲስ አማንያንን ማጥመቃቸው (ከእናት ቤተ ክርስቲያን የወጡትን የከፋ ቦንጋ ሀገረ ስብከት ብቻ ሪፓርት ቢያደርግም)

  • የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴን መጠናከር

  • ሕገ ወጥ ሰባኪያንን እና አጥማቅያንን መቆጣጠር

  • ክህነት የማይገባቸው አላግባብ ክህነት መቀበል ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ተግዳሮት መሆን

  • የቅርስና ንብረት ዘረፋ

  • በየሀገረ ስብከቶቹ ሪፓርት ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን እየሰጠ ያለው መንፈሳዊ አገልግሎት ከተነሱት ዋና ዋና የሥራ ፍሬዎች ናቸው፡፡

ከቀረቡት ሪፓርቶች መካከል ማሳሰቢያ የተሰጠባቸው

33 2nd 2 1ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፡-

“…መስቀል በዓል አከባበር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስ ሆኖ እንደተመዘገበ ሁሉ የመስቀሉ ማኅደር የሆነችው ግሸን ደብረ ከርቤም በዮኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንድትመዘገብ ጥረት እንዲደረግ፣…”

 

 

33 2nd 2 2ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት፡-

“…የክርስቲያን ተደላ ደስታ በመንግሥተ ሰማይ ነው፤ ለሥጋ ተድላ ሲባል ያለ አግባብ ሥልጣነ ክህነት መቀበልና የቤተ ክርስቲያንን ሀብት መመዝበር አምላካዊ ፍርድን ይጠብቃል…”

ማኅበረ ቅዱሳን በ2006 ዓ.ም ከ13,948,984.71 በላይ ወጪ በማድረግ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ደገፈ

ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በ33ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ባቀረቡት ሪፖርትና በዐዋጅ ነጋሪ መጽሔት 6ኛ ዓመት ቁጥር 10 ጥቅምት 2007 ዓ.ም ላይ በተገለጸው ሪፖርት ውስጥ የማኅበረ ቅዱሳን የ2006 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ከነጻ ሞያ አገልግሎት ውጭ ከ13,948.984.7 /አሥራ ሦስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ዐርባ ስምንት ሺሕ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ዐራት ብር/ በላይ ወጪ በማድረግ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት መደገፉ ተገልጿል፡፡

ዋና ዋና ድጋፍ ያደረገባቸው ሀገረ ስብከቶች

ማኅበረ ቅዱሳን በበጀት ዓመቱ ለደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ ለምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት፣ ለደብረ ከዋክብት ጉንዳጉንዶ ገዳም፣ ለሰሜን ምዕራብ ትግራይ ሽሬ አቡነ ቶማስ ገዳም ለውኃ ታንከር፣ ለዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ለምዕመናን መቀመጫ ወንበር ለመግዛት ብር 8,139,847.36 /ስምንት ሚሊዮን አንድ መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ሺሕ ስምንት መቶ ዐርባ ሰባ ብር ከሠላሳ ዘጠኝ ሣንቲም ወጪ በማድረግ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ደግፏል፡፡

በተጨማሪም በተለያዩ አህጉረ ስብከት ለሚገነቡ የአብነት ት/ቤቶችና የካህናት ማሠልጠኛዎች እንዲሁም ለአብነት መምህራንና ተማሪዎች ድጎማና አህጉረ ስብከት ለሚያካሒዷቸው ሥልጠናዎች መደጎሚያ፣ ለምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ግንባታ ብር 11,034,334.00/ አሥራ አንድ ሚሊየን ሠላሳ ዐራት ሺሕ ሦስት መቶ ሠላሳ አራት ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ማኅበሩ በሙያ ደረጃ ለ35 አብያተ ክርስቲያናት የዲዛይን ሥራ ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለመጡ 15 የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች የነጻ የሕግ ምክር አገልግሎት የሰጠ ሲሆን ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለተጠየቀ 10 የልማት ሥራዎች ፕሮጀክት ጥናት በነጻ ተጠንቶ ለጠያቂዎቹ ተሰጥቷል፡፡ በኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ አውታሮች አማካኝነት በሀገር ውስጥና በውጭው ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ሰፊ ትምህርት የሰጠ ሲሆን 671,000.00 /ስድስት መቶ ሰባ አንድ ሺሕ/ ሐመርና ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በበጀት ዓመቱ አሰራጭቷል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎንም በአማርኛ፣ በእንግሊዘኛና በኦሮምኛ ቋንቋዎች በድረ ገጽ ትምህርታዊ ዝግጅቶች እንዲተላለፉ አድርጓል፡፡

ማኅበሩ በበጀት ዓመቱ በ341 የመንግሥትና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሚገኙ 200,000 /ሁለት መቶ ሺሕ/ ኦርቶዶክሳዊ ተማሪዎች ተከታታይ ኮርስ ሰጥቷቸዋል፡፡ በ2006 በጀት ዓመትም 14,847,657.82 /አሥራ አራት ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ ሰባ ሺሕ ስድስት መቶ ሃምሳ ሰባ ብር ከሰማንያ አራት ብር ከሰባ አንድ ሣንቲም ወጪ በማድረግ 848,675.11/ ስምንት መቶ አርባ ስምንት ሺሕ ስድስት መቶ ሰባ አምስት ብር ከአሥራ አንድ ሣንቲም/ በልዩነት ተመዝግቧል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን

  • የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገዳም ሁለገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በብር 4,599,645.00 /አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺሕ ስድስት መቶ ዐርባ አምስት ብር/ ወጪ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡

  • የደብረ ካስዋ ጉንዳጉንዶ ገዳም ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት ዓዲግራት ከተላ ላይ በብር 2,614,431.36 /ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አሥራ ዐራት ሺሕ ዐራት መቶ ሠላሳ አንድ ብር ከሰላሣ ስድስት ሣንቲም/ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡

  • ሰሜን ምዕራብ ትግራይ /ሽሬ/ አቡነ ቶማስ ገዳም 150 ሺሕ ሊትር ውኃ መያዝ የሚችል ውኃ ታንከር በብር 672,822.00 /ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሺሕ ስምንት መቶ ሃያ ሁለት ብር/ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

  • ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የሞጣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን 64 ተማሪዎችን መቀበልና ማስተናገድ የሚችል የአብነት ትምህርት መማሪያ እና ማደሪያ ከነሙሉ መገልገያው በብር 2,950,380.00 /ሁለት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሺሕ ሦስት መቶ ሰማንያ ብር/ ተሠርቶ እና ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

  • በጋሞ ጎፋ ሀገረ ስብከት አርባ ምንጭ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን 100 ተማሪዎችን መቀበልና እና መያዝ የሚችል ማሰልጠኛ በብር 1,666,378.00 /አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ሺሕ ሦስት መቶ ሰባ ስምንት ብር/ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

  • ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በጎንደር በዓታ የአቋቋም ትምህርት ቤት በብር 5,981,132.00 /አምስት ሚሊዮን ብር/ ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

  • በተለያዩ አህጉረ ስብከት 160 የአብነት ት/ቤቶች ለሚገኙ 171 የአብነት መምህራን እና 993 የአብነት ተማሪዎች ከ1,800,000.00 /አንድ ሚሊየን ስምንት መቶ ሺሕ ብር/ በላይ ወጪ ለማዳን ድጎማ ተደርጓል፡፡

  • ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለተጠየቁ የ35 አብያተ ክርስቲያናት የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ዲዛይን ሥራ በነጻ በመሥራት አብያተ ክርስቲያናቱ ሊያወጡ የነበረው ብር 840,000.00 /ስምንት መቶ ዐርባ ሺሕ ብር/ ወጪን ለማዳን ተችሏል፡፡

  • ሀገር ውስጥ ባሉ የተለያዩ አህጉረ ስብከት ከ150 በላይ የሕዝብ ጉባኤያት እና በሰሜን አሜሪካ 5 የስብከተ ወንጌል ጉባኤያት ተደርጎ በርካታ ምእመናን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት እንዲያገኙ ሆኗል፡፡

  • ከሚመለከታቸው አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ፈቃድና ከየአህጉረ ስብከት ጋር በመተባበር ለ10 ቀናት የቆየ ሐዋርያዊ ጉዞ ወደ ምሥራቅ ኢትዮጵያ /አፋር፣ ምሥራቅ ሐረርጌ፣ ድሬዳዋ እና ሶማሌ አህጉረ ስብከት/ ተደርጓል፡፡

  • ስብከተ ወንጌል ያልተስፋፋባቸውን ጠረፋማ አካባቢዎች በመለየት እና ፕሮጀክት በመቅረጽ ስብከተ ወንጌል የማስፋፋት ሥራዎች እየተሠሩ ሲሆን በተሰጠው አገልግሎት ከአህጉረ ስብከት ጋር በመተባበር 4396 ምእመናን ተጠምቀው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ለመሆን በቅተዋል፡፡

  • በሀገሪቱ ባሉት የመንግሥትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ላሉ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን፣ ትውፊትና ነገረ ሃይማኖት ለማወቅ የሚያስችላቸውንና በሥራ ሲሠማሩ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል መነሻ የሚሆናቸውን ትምህርት በካሪኩለም በማካተት ተከታታይነት ያለው የኮርስ ትምህርት ተሰጥቷቸዋል፡፡

33 2007 3

33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተጀመረ

ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

33 2007 3በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ 33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በስብከተ ወንጌል አዳራሽ የተጀመረው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መሪነት ጸሎተ ኪዳን ተደርሶ “ወንድምህ ቢበድልህ ምከረው፣ ይቅር በለው” የሚለው የማቴ.18፡15 ከተነበበ በኋላ ነው፡፡

ከጸሎተ ቡራኬው በመቀጠል የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጣዕመ ዝማሬ አሰምተዋል፡፡

33 2007 2ከዝማሬው በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የመምሪያ ሓላፊ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ ከሀገር ቤትና ከሀገር ውጭ ለመጡት የ33ኛው መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ከአስተላለፉ በኋላ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አቡነ ማቴዎስ ጋባዥነት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የጉባኤውን መከፈት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸውም ትኩረት ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል፡-

  • በቤተ ክርስቲያን ስላለው የመልካም አስተዳደር እጦት

  • የምእመናን ቁጥር መቀነስ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን

  • የሕገወጥ የሰው ልጆች ዝውውር

  • በአፍሪካ ስለተከሰው በሽታ አሳሳቢነትና አደገኛነት

  • በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለሚገኙ ማኅበራት አስመልክቶ ለጉባኤው ገለጻ አድርገዋል፡፡

ከቅዱስ ፓትርያርኩ መግለጫ በመቀጠል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ለ33ኛው የሰበካ33 2007 1 መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች የ2006 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ሪፓርት አቅርበዋል፡፡

 

ለ4 ቀናት በሚቆየው ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኝ ሀገረ ስብከቶች ሪፓርታቸውን አቅርበው ከጨረሱ በኋላ በቀረቡት ሪፓርቶች መነሻነት ውይይት ይደረጋል፡፡

እንደ መርሐ ግብሩ መሠረት በጉባኤው መጨረሻ ቀን ቅዳሜ ጥቅምት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. የጋራ መግለጫ ተነቦ የሽልማትና የምስጋና መርሐ ግብር ከተከናወነ በኋላ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ቃለ ምእዳንና መመሪያ ተሰጥቶ፣ የእራት ግብዣ ከተደረገ በኋላ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው ይጠናቀቃል፡፡

33 2007 4እሑድ ጠዋት ጥቅምት 9 ቀን 2007 ዓ.ም. በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በአጸደ ነፍስ ለሚገኙ ቅዱሳን ፓትርያርኮችና ሊቃነ ጳጳሳት የመታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐትና ቅዳሴ ይከናወናል፡፡

በዕለቱ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የፓትርያርኮችና ሊቃነ ጳጳሳት መታሰቢያ “ዝክረ አበው” በሚል ርእስ በማኅበረ ቅዱሳን የመታሰቢያ እራት ይደረጋል፡፡ከጥቅምት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ይካሔዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡

 

“ቄስ” ገዳሙ ደምሳሽ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ተለዩ

ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም

በዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ

በኑፋቄ ትምህርታቸው ምእመናንን ሲቀስጡና የማኅበረ ካህናቱንና ምእመናኑን አንድነት ሲጎዱ የቆዩት “ቄስ” ገዳሙ ደምሳሽ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ከቅስናና ከቤተ ክርስቲያን ሓላፊነት እንዲሁም ከማንኛውም ክህነታዊ አገልግሎትና ትምህርተ ወንጌል ከመስጠት ታገዱ፡፡

ቋሚ ሲኖዶሱ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ውሳኔውን ያስተላለፈው ግለሰቡ ግልጽ ባልኾነ ሁኔታ የቪዝባደን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ኾነው ከመቀመጣቸው በፊት ወደ ፕሮቴስታንት የእምነት ተቋም ሔደው በቆዩባቸው ጊዜያት ጽፈው ያሳተሟቸው መጻሕፍት ይዘት በሊቃውንት ጉባኤ እንዲመረመር ካደረገ በኋላ መኾኑ በመግለጫው ታትቷል፡፡

 

በተጨማሪም ግልጽ ባልኾነ ሁኔታ ተመልሰዋል ተብሎ በሀገረ ጀርመን ካሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ በኾነው ቪዝባደን ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተሾሙም በኋላ በልዩ ልዩ የጀርመን ግዛቶች እየተዘዋወሩ ሲያስተምሩ የነበረውን ፀረ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት በመቃወም በየጊዜው ከምእመናንና ካህናት የተላኩትን አቤቱታዎች እንደመረመረ መግለጫው ያብራራል፡፡

 

በሊቃውንት ጉባኤው ምርመራ መሠረት ጽሑፎቻቸው ግለሰቡ “የቤተ ክርስቲያናችንን የአብነት ትምህርት በውል ያልተማሩና ምሥጢራትን ያልተረዱ መኾናቸውን” የሚያሳዩ ከመኾናቸው በላይ የተሳሳቱና ኦርቶዶክሳዊ ያልኾኑ የኑፋቄ አስተምህሮዎችን የያዙ ናቸው፡፡ በመኾኑም እነዚህ መጻሕፍት በማንኛውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ እንዳይሠራጩና ለማስተማሪያነትም እንዳይቀርቡ ታዝዟል፡፡ ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ተላልፎ ለደቡብ፣ ደቡብ ምስራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የተላከው ውሳኔ መስከረም 23 ቀን 2007 ዓ.ም በፍራክፈርት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ሰብሳቢነት በተደረገ አጠቃላይ የአድባራት አስተዳዳሪዎችና የሰበካ ጉባኤ ተወካዮች ስብሰባ በውሳኔው የተለዩት ግለሰብም ባሉበት በንባብ መሰማቱን፤ በዚህም ወቅት ግለሰቡ ጉባኤውን ረግጠው መውጣታቸውን መግለጫው ያትታል፡፡ 

 

እኒህ ሰው በሀገረ ጀርመን ሲፈጠሯቸው የነበሩ ችግሮችን አስመልክቶ ከቦታው በሚደርሱን መረጃዎች በመመሥረት በኅትመቶቻችን ስንዘግብ መቆየታችን ይታወሳል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ዝርዝር በሚቀጥለው የስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ እናቀርባለን፡፡

 

33 Sebeka Gubae

33ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡

ጥቅምት 4 ቀን 2007 ዓ.ም.

 በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 33ኛው መደበኛ ስብሰባ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ይካሄዳል፡፡

33 Sebeka Gubaeበመንፈሳዊ ጉባኤው ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ተመድበው ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ የሚገኙ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የመምሪያ ሓላፊዎች፣ የየሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 

sewasew 1

ማኅበረ ቅዱሳን ለሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

sewasew 1

ማኅበረ ቅዱሳን ለአንጋፋውና የሊቃውንት መፍለቂያ ለሆነው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮች፤ ፕሪንተሮችና መጻሕፍት ጥቅምት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለኮሌጁ ደቀመዛሙርት አገልግሎት እንዲውል ድጋፍ አደረገ፡፡

ማኅበሩ ከኮሌጁ በቀረበለት ጥያቄ መሠረት የኮሌጁን ደቀመዛሙርት እውቀት ለማሳደግ የሚያስችሉ ግምታቸው 90 ሺሕ ብር የሚደርሱ 12 ኮምፒተሮች፤ 2 ፕሪንተሮች፤ እንዲሁም ማኅበረ ቅዱሳን በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋዎች ያሳተማቸውን 184 መጻሕፍት በኮሌጁ አዳራሽ ርክክብ አድርጓል፡፡

በርክክቡ ሥነ ሥርዓት ላይ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሓላፊና የኮሌጁ ዋና ዲን ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ ማኅበሩ ያደረገውን ድጋፍ አስመልከቶ ሲገልጹ “ኮሌጁ በርካታ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ያፈራ ነው፡፡ ዛሬም sewasew 2በማፍራት ላይ ቢገኝም በርካታ ችግሮች አሉበት፡፤ በዚህም መሠረት ደቀዛሙርቱ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ሽግግር ጋር ለማገናኘትና ከኢንተርኔት አጠቃቀም አንጻር ያለባቸውን ክፍተት ለመፍታት ለማኅበረ ቅዱሳን ባቀረብነው ጥያቄ መሠረት የኮምፒዩተሮችና የመጻሕፍት ድጋፍ በማድረጉ በመላው የኮሌጁ ማኅበረሰብና ደቀመዛሙርት ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ ማኅበሩ እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነቱ እሰየሠጠ ካለው አገልግሎት አንጻር ወደፊት ተጨማሪ ድጋፎችንም እንደሚያደርግልን ተስፋ አደርጋለሁ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢሆነኝ በበኩላቸው ኮምፒዩተሮችና መጻሕፍቱን ካስረከቡ በኋላ እንደገለጹት “ማኅበሩ ከኮሌጁ በተጠየቀው መሠረት ማድረግ ከሚችለው ውስጥ ትንሹን ነው ያደረገው፡፡ ወደፊትም ኮሌጁ በሚያስፈልገው፤ ማኅበሩ ደግሞ በሚችለው መጠን ድጋፍ ያደርጋል” ብለዋል፡፡

በኮሌጁ ውስጥ ከሚገኙት ሊቃውንት መካከል መምህር ሃይማኖት ኃይለ ማርያም ማኅበሩ ባደረገው ድጋፍ በሰጡት አስተያየት “የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ማድረግ መልካም ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ልጆች በመሆናቸው የቤተ ክርስቲያንን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ነው የሰጡት፡፡ ሌሎችም ማኅበሩን አርአያ አድርገው ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል” በማለት ገልጸዋል፡፡

በኮሌጁ መምህራን የተዘጋጁ መጻሕፍትም ለማኅበረ ቅዱሳን ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እንዲውሉ በመምህራኑ አቅራቢነት፤ በኮሌጁ ዲን አማካይነት ለማኅበረ ቅዱሳን ተበርክቷል፡:

  

jima 2007 3

የጅማ ሀገረ ስብከት ሁለገብ ዘመናዊ ሕንፃ ተመረቀ

መስከረም 27 ቀን 2007 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስስ

jima 2007 3የጅማ ሀገረ ስብከት ያስገነባው ባለ 5 ፎቅ ሁለገብ ዘመናዊ ሕንፃ መስከረም 25 ቀን 2007 ዓ.ም. በቅዱስ ፓትርያርኩና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ፕሬዚዳንት ተመረቀ፡፡

jima 2007ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የልዩ ልዩ መምሪያ ሓላፊዎችና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ክፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን የጅማ ሀገረ ስብከት ከሃያ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አራት ሺሕ ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን ባለ አምስት ፎቅ ዘመናዊ ሁለገብ ሕንፃ ባርከው ሲመርቁ በሰጡት ቃለ ምእዳን “ይህ ሁለገብ ዘመናዊ ሕንፃ በጣም የሚያስደንቅና ለቤተ ክርስቲያናችን ተጨማሪ ሀብት መሆን የቻለ ነው፡፡ ለሌሎች ሀገረ ስብከቶችም ታላቅ ምሳሌና በአርአያነቱም ተጠቃሽ የሚሆን ነው” ብለዋል፡፡

የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ባቀረቡት ሪፖርትም በጅማ ሀገረ ስብከት 308 አብያተ ክርስቲያናት እንደሚገኙና፤ የዚህ ሕንፃ መገንባት ዋነኛ ዓላማ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት አብያተ ክርስቲያናት በካህናትና በበጀት እጥረት jima 2007 2ምክንያት የተቸገሩ በመሆናቸው ሕንፃው ተከራይቶ በሚያስገኘው ገቢ እነዚህን አብያተ ክርስቲያናት በመደገፍ አገልግሎት እንዳይቋረጥ ለማስቻል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ዝርዝሩን እንደደረሰልን እናቀርባለን፡፡

 

meskel 001

በመስቀል በዓል መጨመር ወይም መቀነስ የሌለበት የትኛው ነው?

 መስከረም 20 ቀን 2006 ዓ.ም.

በዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ

meskel 001የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ታሪካዊት እንደ መሆኗ፣ ሁሉም ሃይማታዊ በዓላት ከመንፈሳዊ ባህላዊ ሥርዓቶች ጋር ተሣሥረው እንዲከበሩ መሠረት ናት፡፡ ለዚህ ነው ከሀገራዊና ከሃይማታዊ በዓላት ጋር ተያይዘው የሚከናወኑት መንፈሳዊና ባሕላዊ ሥርዓቶች ምንጫቸው/መነሻቸው/ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ናት የምንለው፡፡ ቀድሞም በኦሪቱ በኋላም በሐዲሱ ሕግጋት ጸንታ የቆየች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ ተዟዙራ አስተምራለች፡፡ ለመስቀሉም ሆነ ለሌሎች ሃይማታዊ በዓላት መነሻቸው የቀደሙት አባቶቻችን ከ4ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ የዘሩት የወንጌል ዘር ነው፡፡

ለዕንቁጣጣሽ (ዐዲስ ዓመት)፣ ለልደት፣ ለጥምቀት እና ለፋሲካ በዓላት ብቻ ሳይሆን ለመስቀል በዓልም ባህላዊ መሠረቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ የመስቀል በዓልን የተመለከትን እንደሆነ በሰሜኑ፣ በደቡቡ፣ በምሥራቁ፣ የሀገራችን ክፍሎች የሚከናወኑት ማናቸውም ባህላዊ ሥርዓቶች መሠረታቸው ፍጹም ሃይማኖታዊ ነው፡፡ ይህም ከላይ እንደተገለጠው የቀድሞ አባቶቻችን በዐራቱም የኢትዮጵያ መዓዝናት እየተዘዋወሩ ወንጌልን የመስበካቸው ውጤት ነው፡፡

የመስቀል በዓል በማይታዩ ወይም በማይዳሰሱ ቅርሶች በዓለም አቀፍ ቅርስነት በዩኔስኮ ከተመዘገበ እነሆ አንድ ዓመት ሞላው፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋር በመሆን ይህን ሃይማኖታዊና ታሪካዊ በዓል በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ስታስመዘግብ ከዚህ በፊት በበዓሉ ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ሃይማታዊና መንፈሳዊ ባህላዊ ሥርዓቶችን አካታ ነው፡፡ የቀነሰችው ወይም የጨመረችው አንዳችም ምዕራባዊ ባዕድ ነገር የለም፡፡

meskel 002በዓሉን ስናከብርም ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በማጉላት ሊሆን ይገባል፡፡ በስመ ዓለማቀፋዊነት ከሃይማኖታዊና ከባህላዊ ሥርዓቶች ውጭ ያሉትን እንደ ርችት መተኮስ፣ ጭፈራና ጩኸት ያሉ ሰርጎ ገብ ድርጊቶችን ወይም ልማዶችን መተው ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ድርጊቶች የበዓሉን ሃይማኖታዊ ይዘት ከመሸርሸራቸው ባለፈ የሀገራችንንም መልካም ገጽታ ስለሚያጎድፉ ነው፡፡

ባዕድ ልማዶችን ከመከላከል አንጻር ከሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ብዙ ይጠበቃል፡፡ በበዓሉ ቀን ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወደ ሀገራችን የሚጎርፉ ቱሪስቶች /ጎብኝዎች/ የኛ የሆነውን ሥርዓት እንጂ እነርሱ የሰለቻቸውን ለማየት አይመጡምና ነው፡፡ ስለዚህ በዓሉን አስመልክቶ በሚቀርቡ ትርኢቶች ላይ የውጭው ዓለም የባሕል ተፅዕኖ እንዳያድርብን መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡meskel 003

ይልቁንስ በብዙ ምእመናን ዘንድ የሚዘወተሩ ለምሳሌ የደመራውን አመድ በትእምርተ መስቀል አምሳል ግንባር ላይ መቀባት፣ ትርኳሹን ወደ ቤት መውሰድ፣ በዕለቱ ከወዳጅ ከዘመድ ጋር መሰባሰብን የመሳሰሉ ከእናት አባቶቻችን የወረስናቸው መንፈሳዊ ድርጊቶች ሊበረታቱና ሊቀጥሉ ይገባል፡፡

ለወደፊትም የበዓሉን ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ሀገራዊ ይዘት ሊያዳክሙ የሚችሉ እንቅስቃሴዎች እንዳይከሰቱ በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጪ የምንኖር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት አባቶች እና ምእመናን እንደ ባለቤት በጋራ በመሆን ለመስቀል በዓል ሥርዓት መጠበቅ የበኩላችንን ድርሻ ልንወጣ ይገባናል፡፡ ባሕላዊው የበዓል አከባበር ሥርዓት ለሃይማታዊው የበዓል አከባበር ሥርዓት መገለጫ ነው እንጅ የሚጨመር ወይም የሚቀነስ ሥርዓት አይኖረውም፡፡

 

 

a tefut 2007 1

መጽሐፈ ጤፉት ለኅትመት በቃች

መስከረም 12 ቀን 2007 ዓ.ም.

መምህር ሳሙኤል ተስፋዬ

a tefut 2007 1የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ግሸን ደብረ ከርቤ መቀመጡንና ሌሎችንም ታሪኮች ያያዘው መጽሐፈ ጤፉት በግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት አማካይነት ከግእዝ ወደ አማርኛ ተተረጉማ ለኅትመት በቃች፡፡

መጸሐፉ በሰባት ምዕራፎች ተከፍሎ የቀረበ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ በዐፄ አምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የነበረውን የግብጻውያንና የኢትዮጵያውያንን ግንኙነት የሚገልጽ ነው፡፡ ሁለተኛው ምዕራፍ በዐፄ ዳዊት አማካይነት ቅዱስ መስቀሉ ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በዐፄ ዳዊት ግዛት ስለመቀመጡ ይናገራል፡፡

ሦስተኛው ምዕራፍ ስለ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብና ቅዱስ መስቀሉን ወደ መስቀለኛው የአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ ስለማስቀመጣቸው በስፋት ይገልጻል፡፡ ዐራተኛው ምዕራፍ ከቅዱስ መስቀሉና መስቀሉ ስለተቀመጠባት የግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ደብር ክብር ጋር ተያይዞ በንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብ የተጻፉት ደብዳቤዎችን አካትቷል፡፡

አምስተኛውና ስድስተኛው ምዕራፎች ግሸን ደብረ ከርቤ ጌታችን በተሰቀለበት በቅዱስ መስቀሉ መክበሩንና ለቦታው ስለተሰጠው ቃል ኪዳን ይዳስሳል፡፡ ሰባተኛውና የመጨረሻው ምዕራፍ መስቀሉ በክብር የተቀመጠበትን የግሸን ደብረ ከርቤ አምባና የአካባቢው ሹማምንት ስለተሰጣቸው ትእዛዛትና ሌሎችንም መረጃዎች ያብራራል፡፡

ሊቀ ሊቃውንት ተክለ ማርቆስ ብርሃኑ የግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ደብር አስተዳዳሪ ስለ መጽሐፉ መታተም ሲገልጹ “መጽሐፈ ጤፉት ለበርካታ ዓመታት የቤተክርስቲያናችንን የታሪክ፣የቀኖና፣ የሥርዐትና ሌሎችም ሰነድ ይዛ በክብር ተጠብቃ የቆየችና በየዓመቱ በውስጧ የዘችው ቃልኪዳን እየተነበበ የኖረ ሲሆን አሁን ታትሞ ለምዕመናን እንዲደርስ መደረጉ የሀገርንና የቤተክርስቲያን ታሪክ አውቀን ሥርዐቱንና ቃል ኪዳኑን ጠብቀን ለቦታው የሚገባውን ክብር እንድንሰጥ ያስችላል፡፡” ብለዋል፡፡

a tefut 2007 2መጽሐፈ ጤፉት በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ አማካይነት እንደተጻፈና በየዓመቱ፤ በተለይም በመስከረም 21 እና መጋቢት 10 ቀን የመስቀሉ አመጣጥና በግሸን ደብረ ከርቤ ስለተሰጠው ቃል ኪዳን በመተርጎም ለምእመናን ይሰማል፡፡

መጽሐፈ ጤፉትን ማግኘት የሚፈልጉ በግሸን ደብረ ከርቤና በአዲስ አበባ በ0911238610፣ 0911616880 በመደወል ማግኘት እንደሚቻል ከመጽሐፉ የኅትመት አስተባባሪዎች ለመረዳት ተችሏል፡፡