33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተጀመረ

ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

33 2007 3በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ 33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በስብከተ ወንጌል አዳራሽ የተጀመረው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መሪነት ጸሎተ ኪዳን ተደርሶ “ወንድምህ ቢበድልህ ምከረው፣ ይቅር በለው” የሚለው የማቴ.18፡15 ከተነበበ በኋላ ነው፡፡

ከጸሎተ ቡራኬው በመቀጠል የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጣዕመ ዝማሬ አሰምተዋል፡፡

33 2007 2ከዝማሬው በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የመምሪያ ሓላፊ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ ከሀገር ቤትና ከሀገር ውጭ ለመጡት የ33ኛው መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ከአስተላለፉ በኋላ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አቡነ ማቴዎስ ጋባዥነት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የጉባኤውን መከፈት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸውም ትኩረት ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል፡-

  • በቤተ ክርስቲያን ስላለው የመልካም አስተዳደር እጦት

  • የምእመናን ቁጥር መቀነስ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን

  • የሕገወጥ የሰው ልጆች ዝውውር

  • በአፍሪካ ስለተከሰው በሽታ አሳሳቢነትና አደገኛነት

  • በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለሚገኙ ማኅበራት አስመልክቶ ለጉባኤው ገለጻ አድርገዋል፡፡

ከቅዱስ ፓትርያርኩ መግለጫ በመቀጠል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ለ33ኛው የሰበካ33 2007 1 መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች የ2006 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ሪፓርት አቅርበዋል፡፡

 

ለ4 ቀናት በሚቆየው ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኝ ሀገረ ስብከቶች ሪፓርታቸውን አቅርበው ከጨረሱ በኋላ በቀረቡት ሪፓርቶች መነሻነት ውይይት ይደረጋል፡፡

እንደ መርሐ ግብሩ መሠረት በጉባኤው መጨረሻ ቀን ቅዳሜ ጥቅምት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. የጋራ መግለጫ ተነቦ የሽልማትና የምስጋና መርሐ ግብር ከተከናወነ በኋላ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ቃለ ምእዳንና መመሪያ ተሰጥቶ፣ የእራት ግብዣ ከተደረገ በኋላ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው ይጠናቀቃል፡፡

33 2007 4እሑድ ጠዋት ጥቅምት 9 ቀን 2007 ዓ.ም. በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በአጸደ ነፍስ ለሚገኙ ቅዱሳን ፓትርያርኮችና ሊቃነ ጳጳሳት የመታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐትና ቅዳሴ ይከናወናል፡፡

በዕለቱ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የፓትርያርኮችና ሊቃነ ጳጳሳት መታሰቢያ “ዝክረ አበው” በሚል ርእስ በማኅበረ ቅዱሳን የመታሰቢያ እራት ይደረጋል፡፡ከጥቅምት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ይካሔዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡