33 Sebeka Gubae

33ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡

ጥቅምት 4 ቀን 2007 ዓ.ም.

 በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 33ኛው መደበኛ ስብሰባ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ይካሄዳል፡፡

33 Sebeka Gubaeበመንፈሳዊ ጉባኤው ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ተመድበው ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ የሚገኙ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የመምሪያ ሓላፊዎች፣ የየሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡