33 2nd 2 1

33ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው እንደቀጠለ ነው፡፡

ጥቅምት 6 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 5 ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም የተጀመረው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ቀጥሏል፡፡ በጥቅምት 5 ቀን የከሰዓት ውሎና ጥቅምት 6 ቀን ጠዋት 24 አህጉረ ስብከቶች ሪፓርቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡

ከቀረቡት ሪፓርቶች በዋናነት ትኩረት የሳቡት

  • ለልማት ሥራ ትኩረት መሰጠቱ

  • አዳዲስ አማንያንን ማጥመቃቸው (ከእናት ቤተ ክርስቲያን የወጡትን የከፋ ቦንጋ ሀገረ ስብከት ብቻ ሪፓርት ቢያደርግም)

  • የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴን መጠናከር

  • ሕገ ወጥ ሰባኪያንን እና አጥማቅያንን መቆጣጠር

  • ክህነት የማይገባቸው አላግባብ ክህነት መቀበል ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ተግዳሮት መሆን

  • የቅርስና ንብረት ዘረፋ

  • በየሀገረ ስብከቶቹ ሪፓርት ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን እየሰጠ ያለው መንፈሳዊ አገልግሎት ከተነሱት ዋና ዋና የሥራ ፍሬዎች ናቸው፡፡

ከቀረቡት ሪፓርቶች መካከል ማሳሰቢያ የተሰጠባቸው

33 2nd 2 1ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፡-

“…መስቀል በዓል አከባበር በዮኔስኮ የዓለም ቅርስ ሆኖ እንደተመዘገበ ሁሉ የመስቀሉ ማኅደር የሆነችው ግሸን ደብረ ከርቤም በዮኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንድትመዘገብ ጥረት እንዲደረግ፣…”

 

 

33 2nd 2 2ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት፡-

“…የክርስቲያን ተደላ ደስታ በመንግሥተ ሰማይ ነው፤ ለሥጋ ተድላ ሲባል ያለ አግባብ ሥልጣነ ክህነት መቀበልና የቤተ ክርስቲያንን ሀብት መመዝበር አምላካዊ ፍርድን ይጠብቃል…”