ማኅበረ ቅዱሳን «ደጀ ሰላም»ብሎግ ልሣኑ አለመሆኑን አስታወቀ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ፣ «ደጀ ሰላም» በሚሰኝ ብሎግ ላይ የሚለቀቀው መግለጫ እንደማይመለከተው አስታወቀ፡፡

የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ ብሎጉ «የማኅበረ ቅዱሳን ልሳን ነው» የሚል መረጃ ባልታወቁ አካላት መሰራጨቱንና በዚህም ምክኒያት ጉዳዩን አስመልክቶ ተደጋጋሚ ጥያቄ በስልክና በኢሜል እንደቀረበላቸው ገልጸዋል፡፡

ዋና ጸሐፊው ብሎጉ የማኅበረ ቅዱሳን እንዳልሆነና ማኅበሩ በዚህ ብሎግ መረጃ እንደማያስተላልፍ ምዕመናን እና የቤተ ክርስቲያን አካላት ሁሉ እንዲያውቁ አሳስበዋል፡፡

 
 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር