Entries by Mahibere Kidusan

የምሕረት ቤት

የፍቅር ባለቤት፣ የምሕረት ጌታ፣ የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት፣ የሰው ልጆች ቤዛ ጌታችን በተወለደባት በኢየሩሳሌም ከተማ በቤተ መቅደሱ አቅራቢያ የምትገኝ በዕብራይስጥ ቋንቋ “ቤተ ሳይዳ” በአማርኛው ደግሞ “የምሕረት ቤት” የተባለች የመጠመቂያ ቦታ ነበረች፡፡

መፃጒዕ

ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል በደዌ ዳኛ፣ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ የኖረ መፃጉዕን በአልጋው ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቀርቦ “ባድንህ ፈቃድህ ነውን?” አለው።ቅዱስ ጳውሎስ “የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል…” ብሎ የመሰከረለት ጌታችን ፈውስን በመጠባበቅ ላይ የነበረውን ይህን ሰው አይቶ ፈቃዱን እያወቀ ግን ፍቀድልኝና ላድንህ አለው።

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፉት ሁለት ክፍሎች ‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ›› በሚል ርእስ ጽሑፍ አድርሰናችኋል፡፡ አንብባችሁ ቁም ነገር እንዳገኛችሁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ አሁን ደግሞ ክፍል ሦስትን ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!

ምኵራብ፡- የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት

“ቦአ ኢየሱስ ምኵራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት፤ አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት፤ እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤ የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው።” (ጾመ ድጓ)

የእግዚአብሔር ባሕርያት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን!  እንኳን ለታላቁ ዐቢይ ጾም አደረሳችሁ! በዚህ ጊዜ ግን ልጆች ከሰባት ዓመት ጀምሮ መጾም እንደሚጀመር እናስታውሳችሁ! መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፡፡ ባለፈው “ሀልዎተ እግዚአብሔር” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ የእግዚአብሔር ባሕርያት ምን እንደሆኑ እንማራለን!-

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ!››

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ሳምንት ‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ›› በሚል ርእስ ባቀረብንላችሁ ጽሑፍ ቤተ ክርስቲያን ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዴት እየተላለፈች ወደ እኛ  እንደደረሰችና እኛም እንዴት ከአባቶቻችንና እናቶቻችን እንደተረከብናት በጥቂቱ የዳሰስንበትን ክፍል አድርሰናችኋል፡፡ በዚህ በክፍል ሁለት ደግሞ ከክፍል አንድ የቀጠለውንና “ቤተ ክርስቲያንን እኛስ እንዴት ለቀጣዩ ትውልድ እናስተላልፋት?፡ የሚለውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!

‹‹ዕለት ዕለት የሚያሳስበኝ የቤተ ክርስቲያን ነገር ነው›› (፪ኛ ቆሮ.፲፩፥፳፰)

ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ቃል የተናገረው ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው መልእክቱ ነው፡፡ ዕለት ዕለት ጽኑ የሆኑ መከራዎች ያጋጠሙት ቢሆንም ያ ሁሉ ሳያሳስበው፣ ሳይከብደውና ሳያስጨንቀው በመዓልትም በሌሊትም ዕረፍት የሚነሣው የቤተ ክርስቲያን ነገር ነበር፡፡ የተጠራው ለቤተ ክርስቲያን እንዲያስብና እንዲያገለግል በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ የደረሱበትን ችግሮች ሁሉ ገለጸላቸው፡፡

ቅድስት፡ የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት

የቅድስና ባለቤት የሆነው እርሱ እግዚአብሔር አምላክ ነው። እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እባረክ አይል ቡሩክ ነው። በእርሱ የባሕርይ ቅድስና እኛን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ቡሩክ ሆኖ ባረከን፣ ቅዱስ ሆኖ ቀደሰን፣ሕያው ሆኖ ሕያዋን አደረገን። የጸጋ ቅድስናንም ከእርሱ አገኘን።

የምን አለበት መዘዝ!

“በምን አለበት” ሰበብ ከእግዚአብሔር ሕግና ትእዛዝ ልንወጣ አይገባም፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እንደ ርግብ የዋህ፣ እንደ እባብ ልባሞች (ብልጦች) ሁኑ” ያለው ያልተገባ የዋህነት ስለሚጎዳ ነው፤ ብዙ የዋሃን በየዋህነት ሃይማኖታቸውን የለቀቁ አሉ፡፡ እኛን ግን እግዚአብሔር አምላካችን በሃይማኖትና በምግባር ያጽናን፡፡

የምን አለበት መዘዝ!

በዚህ ቃል ብዙዎች ሕይወታቸው ተጎድቷል፤ ሃይማኖታቸውም እንዲሁ፤ ለምሳሌ “ባንጾም ምን አለበት? እግዚአብሔር ምን ሠራችሁ እንጂ ምን በላችሁ አይለንም” የሚሉ አሉ፤ “መስቀል ባንሳለም ምን አለበት? ወደ ቤተ ክርስቲያን ባንሄድ ምን አለበት? እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ አለ” የሚሉ ሰዎችም አሉ፤ ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ከሕዝባችን ባህል ውጪ “በምን አለበት” የሚጓዙ ሰዎች ጥቂቶች አይደሉም።፡