በዳዊት አብርሃም
- ጥቅሱን ከዓውዱ ነጥሎ መጥቀስ
አንድን ጥቅስ በተሟላ መልኩ በትክክል ጠቅሶ ድምዳሜ ላይ መድረስ ትክክል ባይሆን እንኳ የተሻለ ነገር አያጣውም፡፡ ስሕተቱን የከፋ፣ የስሕተት ስሕተት የሚያደርገው አንዲቷን ጥቅስ ቆንጽለው ሲጠቅሷት ነው፡፡ ብዙዎች መናፍቃን አንድን ጥቅስ አሟልተው ለመረዳት ጥቂት መስመሮችን ከፍ ብለው እንዲሁም ከጠቀሱት ጥቅስ ቀጥሎ ያሉትን ጥቂት ዐረፍተ ነገሮች ጨምረው ለመመልከት ቢሞክሩ ድምዳሜያቸውን ርግፍ አድርገው መተው ወይም የሚያሰሙትን ተቃውሞ ባልደገሙት ነበር፡፡
ይህንም በሚቀጥሉት ስለ ነገረ ድኅነት ከተጻፉት ጥቅሶች አንጻር እንመልከት፡፡ “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፡፡” (ኤፌ2፡8-9) የዚህ ጥቅስ መልእክት በጣም ግልጽ ይመስላል፤ ጥቅሱ ‹ሥራ አያስፈልግም፣ እምነትና ጸጋ ብቻቸውን ለመዳን በቂ ናቸው› የሚል መልእክት የያዘ መስሎ ይታያል፡፡ ግን ሳንቸኩል አንድ ቁጥር ወረድ ብለን ንባባችንን ብንቀጥል እንዲህ የሚል እገኛለን፡፡ “እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” (ኤፌ2፡10)
Read more