• እንኳን በደኅና መጡ !

ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ጥቅሙና ጉዳቱ

ከመምህር ሓጋዚ አብርሃ ባለንበት ዘመን ማኅበራዊ ሚዲያ በወጣቱ መንፈሳዊ ሕይወት፣ ሥነ ምግባር፣ ሥርዓተ ትምህርት እና ሥነ-ልቡናዊ ሕይወት ላይ እያሳደረ ያለው ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው። ማኅበራዊ ሚዲያ በራሱ መሣሪያ ነው፤ መሣሪያ ደግሞ እንደ አጠቃቀማችን ወይ ይገነባናል ወይም ያፈርሰናል። “ከአያያዝ ይቀደዳል ከአነጋገር ይፈረዳል” እንዲሉ አበው አእምሮ ያለን አገናዛቢ፣ ልብም ያለን አሳቢ ፍጡር ነን። ከዚህ የተነሣ ይጠቅሙናል፣ ድካማችንን ይቀንሱልናል […]

“በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው” (ሐዋ. ፪ ፥፬)

ከመምህር ተፈሪ መንገሻየተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች እንደምን ሰነበታችሁ? አሜን፣ የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን። እንኳን ለበዓለ ሃምሳ (በዓለ ጰራቅሊጦስ) አደረሳችሁ።ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ላይ እንደጻፈልን፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ለዓርባ ቀናት ለደቀ መዛሙርቱ እየተገለጠ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ነገራቸው። በዓርባኛው ቀን ሲያርግ እንዲህ አላቸው፦ “ወናሁ አነ እፌኑ ተስፋሁ ለአቡየ ላዕሌክሙ ወአንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም […]

ደብረ ምጥማቅ

ከመምህር አዲሱ በዛብህ ​”አብ በሰማይ ሆኖ ተመለከተ፣ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም፤ አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ።”[ቅዳሴ ዘእግዚእትነ ማርያም]ደብረ ምጥማቅ ከሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓላት አንዱ ነው። ደብረ ምጥማቅ በግብፅ ሀገር በምኔተ ገምኑዲ አቅራቢያ የምትገኝ ቦታ ናት። እመቤታችን በስደት ሳለች ጌታ በዚህ ቦታ በስምሽ ዐቢይ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል ብሎ […]

ማስታወቂያ

ማስታወቂያ

በማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ አገልግሎቱን በማጠናከር በግቢ ጉባኤያት ላይ ውጤታማ ሥራ ለመሥራትና ብቁ አገልጋዮችን ለማፍራት ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቶቹን ለማስፈጸም ይረዳውም ዘንድ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ትኬት ሽያጭ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በማሠራጨት ላይ ይገኛል፡፡ እርስዎም ትኬቱን በመግዛት ትውልድን ለመቅረጽ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሻራዎን ያኑሩ፡፡

ጉባኤ-ቃና መጽሔት-ነሐሴ-2016-ዓ.ም

ጉባኤ-ቃና መጽሔት-ነሐሴ-2016-ዓ.ም

መልእክትዎን ይላኩልን