ማስታወቂያ
ማስታወቂያ

በማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ አገልግሎቱን በማጠናከር በግቢ ጉባኤያት ላይ ውጤታማ ሥራ ለመሥራትና ብቁ አገልጋዮችን ለማፍራት ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቶቹን ለማስፈጸም ይረዳውም ዘንድ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ትኬት ሽያጭ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በማሠራጨት ላይ ይገኛል፡፡ እርስዎም ትኬቱን በመግዛት ትውልድን ለመቅረጽ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሻራዎን ያኑሩ፡፡
ጉባኤ-ቃና መጽሔት-ነሐሴ-2016-ዓ.ም
ጉባኤ-ቃና መጽሔት-ነሐሴ-2016-ዓ.ም
በዓለ ደብረ ታቦር!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዐሥሩን ደቀ መዛሙርት በእግረ ደብር ትቶ ሦስቱን የምስጢር ደቀ መዛሙርት የተባሉትን ቅዱስ ጴጥሮስን፣ ቅዱስ ዮሐንስንና ቅዱስ ማርቅዱስን ይዞ ወደ ደብረ ታቦር ተራራ የወጣበትና በዚያም ከመቃብር ሊቀ ነቢያት ሙሴን፣ ከብሔረ ሕያዋን ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን አምጥቶ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት በማሰብ ነሐሴ ፲፫ ቀን በየዓመቱ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ ደብረ […]
ክረምትና የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች
የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ለመደበኛው ትምህርት ራሳቸውን በማዘጋጀት በውጤት ታጅበው ለሚቀጥለው ዓመት ለመሸጋገር አቅማቸውን ሁሉ ተጠቅመው ጊዜአቸውን ሰጥተው ሲተገብሩ ማየት የተለመደ ነው፡፡ “የሚተክልም የሚያጠጣም አንድ ናቸው፤ ሁሉም እንደ ድካማቸው ዋጋቸውን ይቀበላሉ” (፩ኛ ቆሮ. ፫፥፰) ተብሎ እንደተጻፈው ድካሙ ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን በራስ ጥረት ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔርም ፈቃድና ድጋፍ እንደሚያስፈልግ መረዳት ይገባል፡፡ “እኔ የወይን ግንድ ነኝ፤ ቅርንጫፎቹም […]
ፅንሰታ ለማርያም
ቅደስት ቤተ ክርስቲያናችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበትን ዕለት ነሐሴ ፯ ቀን በየዓመቱ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች በእናቷ ሐና በኩል ቅድመ አያቶቿ ጴጥሪቃና ቴክታ ደጋጐችና እግዚአብሔርን የሚፈሩና በፍጹም ልቡናቸው እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔርን ማምለክ ብቻ ሳይሆን በባለጠግነታቸውም የታወቁ ነበሩ፡፡ ነገር ግን ልጅ ስላልነበራቸው በጣም ያዝኑና ይተክዙ ስለነበር አንድ ቀን ጰጥሪቃ የሀብቱን ብዛት […]