• እንኳን በደኅና መጡ !

ወርኀ ጽጌ

ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ቀን ድረስ ያለው ወቅት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዘመነ ጽጌ ወይም ወርኀ ጽጌ ተብሎ ይጠራል፡፡ ክረምቱ አልፎ ሰማዩ የሚጠራበት፣ የምድር አበቦች የሚፈኩበትና የሚደምቁበት፣ ሜዳውና ሸንተረሩ ልምላሜ የሚላበሱበት፣ ወንዞች የሚጠሩበትና ለፍጥረታት ሁሉ ተስማሚ አየር የሚነፍስበት ጊዜ ነው፡፡    ይህ ወቅት ሄሮድስ ከእኔ ሌላ ንጉሥ እስራኤልን ማን ሊገዛ ይችላል? በሚል በይሁዳ ክፍል በቤተ […]

በዓለ መስቀል

በመ/ሰላምቀሲስደጀኔሺፈራው (ከአሜሪካ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመስቀልን በዓል የምታከብረው መስከረም ፲፯ እና መጋቢት ፲ ቀን ነው። እነዚህም አይሁድ በክፋት ቀብረው ሠውረውት የነበረውን መስቀል ለማግኘት ቁፋሮ የተጀመረበት እና መስቀሉ የተገኘበት ዕለታት ናቸው። ክቡር መስቀሉ ከክርስቲያኖች ተሰውሮ የኖረው ለሦስት መቶ ዓመታት ነው። ክቡር መስቀሉ እንዴት ሊጠፋ ቻለ? መስከረም ፲፮ እና ፲፯ የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር፦ በክፋት የተመሉ […]

“የቀደመውም አለፈ፤ እነሆ ሁሉም አዲስ ሆነ” (፪ቆሮ. ፭፥፲፰)

እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን፡፡ መልካም አዲስ ዓመት! በኢትዮጵያውያን ዘመን አቆጣጠር የመስከረም ወር የወራት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ ይህ ወር ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ ገበሬው በክረምቱ ወራት መሬቱን አልስልሶ፣ ዘሩንም ዘርቶ ምድሪቱም አደራዋን ለመመለስ በልምላሜ የምታጌጥበት ወር ነው፡፡ በዚህም ምክንያት እንስሳት ለምለሙን ሣር ግጠው፣ የጠራውን ውኃ ጠጥተው ረክተው፣ አምረው የሚታዩበት […]

ማስታወቂያ

ማስታወቂያ

በማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ አገልግሎቱን በማጠናከር በግቢ ጉባኤያት ላይ ውጤታማ ሥራ ለመሥራትና ብቁ አገልጋዮችን ለማፍራት ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቶቹን ለማስፈጸም ይረዳውም ዘንድ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ትኬት ሽያጭ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በማሠራጨት ላይ ይገኛል፡፡ እርስዎም ትኬቱን በመግዛት ትውልድን ለመቅረጽ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሻራዎን ያኑሩ፡፡

ጉባኤ-ቃና መጽሔት-ነሐሴ-2016-ዓ.ም

ጉባኤ-ቃና መጽሔት-ነሐሴ-2016-ዓ.ም

መልእክትዎን ይላኩልን