መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ሥርጭት አንደኛ ዓመት ተከበረ
መጋቢት 2 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ሥርጭት አንደኛ ዓመት በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ ባለሀብቶች፣ አርቲስቶች የማኅበሩ ደጋፊዎችና የማኅበሩ የሥራ አመራር አባላት በተገኙበት ተከበረ፡፡
በዕለቱ የቴሌቭዥን ሥርጭቱን አንደኛ ዓመት ለማክበር የተገኙትን ባለድርሻ አካላት “እንኳን ደኅና መጣችሁ” ያሉት የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሰሙ ምትኩ እንደገለጹት “ማኅበረ ቅዱሳን ወንጌለ መንግሥትን ለዓለም ለማዳረስ በሚደረገው መንፈሳዊ አገልግሎት የኅትመት ውጤቶች ሲጠቀም መቆየቱን ገልጸው አሁንም በቴክኖሎጂው በመታገዝ በዓለም ሁሉ ከምንደርስበት መንገዶች አንዱ የቴሌቪዥን መርሐ ግብሩ መጀመር የምሥራች ሲሆን በእውቀት፣ በገንዘብ፣ በጉልበት ድጋፋችሁ ሁል ጊዜ የማይለየን ክቡራን እንግዶቻችን አሁንም ድጋፋችሁ እንዳይለየን በሚል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የደሴ ማእከል ቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል ስለቤተክርስቲያን ዘላቂ ልማት ከበጎ አድራጊዎች ጋር ውይይት አደረገ፡፡
የካቲት 28 ቀን 2006 ዓ.ም.
ወርቁ በላይሁን ደሴ ማእከል
የደሴ ማእከል ቅዱሳት መካናትና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል “ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት በጋራ እንሥራ” በሚል መርህ ለሁለተኛ ጊዜ ከደሴ ከተማ በጎ አድራጊዎች ጋር የካቲት 23 ቀን 2006 ዓ.ም ውይይት አደረገ፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ
ጥሪ የተደረገላቸው በጎ አድራጊዎች የተገኙ ሲሆን፤ ለዘላቂ የቤተ ክርስቲያን ልማት መሠራት ስለሚገባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውይይት ተደርጓል፡፡
ምኲራብ
የካቲት 27 ቀን 2006 ዓ.ም.
ታመነ ተ/ዮሐንስ
“ዘወትርም በቤተ መቅደስ ያስተምር ነበር” ሉቃ.19፥47
ምኲራብ የአይሁድ የጸሎት ቤት ሲሆን በብሉይ ኪዳን ዘመን የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተ መቅደስና በሥርዓቱ የተመሠረተ ነበር፡፡ ናቡከደነጾር ግን ቤተ መቅደሱን አፈረሰ ሕዝቡንም ወደባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚያም ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማኅበረተኛነት ልዩ ቤት ሊሠሩ እንደጀመሩ ይታሰባል፡፡ /የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት/
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በዓለ ሢመት ተከበረ::
የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርእስ ጥናት አቀረበ
የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርዕስ በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ዋና ክፍል አዘጋጅነት በአቶ አለማ ሐጎስ አቅራቢነትና በአቶ አበባው አያሌው አወያይነት በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም ቀረበ፡፡
ማእከሉ ወደ ሲሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ጉዞ ሊያካሂድ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የካቲት 20 ቀን 2006 ዓ.ም.
ከአርባ ምንጭ ማእከል
በማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማእከል መራሔ ፍኖት በሚል መሪ ቃል ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መጋቢት 21 ቀን 2006 ዓ.ም ወደ ሲሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ጉዞ ያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎቱን ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገለጸ፡፡
የካቲት 18 ቀን 2006 ዓ.ም.
በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ንዑስ ክፍል ለቤተ ክርስቲያን እና ለማኅበሩ አገልግሎት ጠቃሚ የሆኑ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና አሠራሮችን በቀላሉ ለማቅረብ የተቁዋቁዋመ ክፍል ነው። ይህ ክፍል ከ1999 ዓ.ም (2008) ጀምሮ በሰሜን አሜሪካ ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ከንዑስ ክፍሉ ባገኘነው መረጃ መሠረት ክፍሉ፡-
ጥናትና ምርምር የጥናት ጉባኤው ሊያካሂድ ነው
የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
በታመነ ተ/ዮሐንስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርእስ ጥናታዊ ጽሑፍ ሊያዘጋጅ ነው፡፡
«ተዋሕዶ ለአንድሮይድ» የተሰኘ የስልክ ላይ አገልግሎት ተጀመረ
የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዝግጅት ክፍሉ ሪፖርተር
ሐዊረ ሕይወት ወደ አዲስ ዓለም ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊካሄድ ነው
የካቲት 14 ቀን 2006 ዓ.ም.
ዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ
በዚህ ዓመት ለሁለተኛ ጊዜ የታሰበው ሐዊረ ሕይወት ወደ ርእሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን መጋቢት 21 ቀን 2006 ዓ.ም ሊካሄድ መሆኑን፤ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ገለጹ፡፡