በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎቱን ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገለጸ፡፡

የካቲት 18 ቀን 2006 ዓ.ም.

በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ንዑስ ክፍል ለቤተ ክርስቲያን እና ለማኅበሩ አገልግሎት ጠቃሚ የሆኑ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና አራሮችን በቀላሉ ለማቅረብ የተቁዋቁዋመ ክፍል ነው። ይህ ክፍል ከ1999 ዓ.ም (2008) ጀምሮ በሰሜን አሜሪካ ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ከንዑስ ክፍሉ ባገኘነው መረጃ መሠረት ክፍሉ፡-

  1.  የሰሜን አሜሪካ ዋና ማእከል የሚጠቀምበትን ዋና የትምሕርት ፣የዜና፣ የማስታውቂያ፣ ዌብ ሳይት አዘጋጅቷል (Mkus.org)

  2.  ለገዳማት እና አድባራት መርጃ የሚሆን ገንዘብ ማስገኛ እና ሪፖርት ማድረጊያ (ኢንተራክቲቭ) ዌብ ሳይት አዘጋጅቶ በአገልግሎት ላይ እንዲውል አድርጓል (Gedamat.org)

  3. የአባላትን መመዝገቢያ እና መቆጣጠሪያ ሶፍትዌር ሰርቶ በስራ አውሟል http://us.mahiberekidusan.org/Login.aspx

  4.  የአብያተ ክርስቲያናት አድራሻ ማግኛ ዌብ ሳይት ሰርቶ ለተገልጋዮች ምእመናን አቅርቧል (Eotc.info)

  5. የእቅድ እና ሪፖረት ማቅረቢያ ዌብ ሳይት አዘጋጅቶ ለአገልግሎት አውሏል (plar.mkus.org)

  6. ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ አባላት ለማስተዳደር የሚረዳ ዘዴ (ሲሰትም) አዘጋጅቷል

  7.  የዝቋላ ቤተ ክርስቲያን ለጊዚያዊ መርጃ የሚሆን የፔፓል ዌብ ሳይት አዘጋጅቶ ገንዘብ የሚሰበሰብበትን መንገድ አፋጥኗል

  8. የተዋሕዶ ቴሌቪዥን (Eotc.tv) የሚጠቀምበትን ዌብ ሳይት በማዘጋጀት መነፈሳዊ የቴሌቭዥን ዝግጅቶችን ለማስተላለፍ ችሏል

  9. ለጥናትና ምርምር የሚጠቅሙ ዌብ ሳይቶች (Servey websites) በቀላሉ መስራት የሚያስችል አቅም ፈጥሯል

  10. አባላት መወያየት የሚችሉበት ማኅበራዊ ዌብ ሳይት ፈጥሯል፡፡ (http://www.eotcworld.org/)

  11. የቤተ ክርስቲያንን የቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) በዌብ ላይ ሰርቶ አቅርቧል http://www.eotc.info/calendar

  12. እነዚህን የተሠሩ ሥራዎች ሁሉ አባላት በአንድ ቦታ ላይ እንዲያገኙዋቸው በሚያስችል መልኩ http://www.mahiberekidusan.org/portal/ አስቀምጧል።

  13. የአይፎን ስልክ አፕሊኬሽኖች (የቤተ ክርስቲያን ማውጫ፣ የቴሌቪዠን እና የዜና፣ የቅዱሳን መጻሕፍት፣ተዋሕዶ ሚድያ፣ ግጻዌ፣ ቀን መቁጠሪያ፣ ቀን መለወጫ፣ የእልቱን ምንባብ ማውጫ) ሰርቶ አውጥቶአል። 

  14. ለማኅበሩ በአጠቃላይ የሚያገለግል አዲስ እና ተመሳሳይነት ያለው የኢሜል አድራሻ አዘጋጅቶ በሰሜን አሜሪካ በሁሉም ደረጃ ያሉ ክፍሎች እንዲጠቀሙ ማድረግ ጀምሯል።

  15.  አብያተ ክርስቲያናት የራሳቸውን ዌብ ሳይት እንዲሰሩ የሚያስችል ቴምፕሌት አዘጋጅቶአል። ከአብያተ ክርስቲያናት በተጠየቀ ቁጥር በአግልግሎት ላይ እንዲውል ያደርጋል።

  16. ከአባላት ግንኙነት ክፍል ጋር በመተባበር የአባላትን መቆጣጠሪያ ሶፍትዌር ሊጨምር የሚገባቸውን መረጃዎች መጨመር እና ለተፈጠሩ ችግሮች መፍትሔ መፈለግ ችሏል፡፡

 

በመሠራት ላይ ያሉ፡-

  1. የሽያጭ አገልግሎት (ሐመር፣ ስምዓ ጽድቅ፣ አልባሳት…)የሚሰጥ ዌብ ሳይት መስራት (ለልማት ክፍል)

  2. ለአንድሮይድ እና ለዊንዶውስ ስልኮች የሚሆን አፕሊኬሽኖች (የቤተ ክርስቲያን ማውጫ፣ የቴሌቪዠን እና የዜና፣ የቅዱሳን መጻሕፍት፣ የአባላት መሰረታዊ መረጃ፣ ተዋሕዶ ሚድያ፣ ግጻዌ፣ ቀን መቁጠሪያ፣ ቀን መለወጫ፣ የእልቱን ምንባብ ማውጫ) መስራት።

  3.  ጉባኤ ቤት ወይም የዜማ ማጥኛ ዌብ ሳይት ማዘጋጀት

  4.  አባላት ስልጠና (Members training) እና የርቀት ትምህርት (Virtual campus) መስጫ ሶፍትዌር ወይም ዌብ ሳይት መሥራት 

  5. ሕፃናትን ማእከል ያደረገ ለትምህርት አገልግሎት የሚሆን ዌብ ሳይት መሥራት

  6. ክፍሉ የሚያስተዳድራቸውን ሰርቨሮች አቅም ማሻሻል፣ የሚያዙ ዳታዎች (data) በትክክል ግልባጭ (backup) እንዲኖራችው ማደረግ እና ችግር ሲኖር ማገገም የሚችሉብት ዘዴ (disaster recovery plan) ቀድሞ ማዝጋጀት

  7.  የቤተ ክርስትያን ትምህርት፣ መዝሙራት፣ ድራማዎች፣ እና ሌሎች ቪድዮዎች በቀላሉ የሚገኙበት (EOTC tube) ዌብ ማዘጋጀት

  8. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የ81ዱ (ሰማንያ አሐዱ) መጸሐፍ ቅዱስን በድምፅ (በንባብ) ማዘጋጀት

    የሚሉት ሥራዎች ይገኙበታል።

 

በአጠቃላይ ክፍሉ ከተቋቋመ ጀምሮ ያበረከታቸው አገልግሎቶች የሚያስመሰግኑ እና በ2004 በሚኒሶታ በተደረገው ጉባኤ ሽልማት ያገኘበት ሲሆን ቤተ ክርስቲያናችን እና ማኅበራችን በዚህ የቴክኖሎጂ ዘርፍ ማግኘት የሚገባቸውን ስናነጻጽረው የተሰሩት ስራዎች አበረታች ጅምሮች እንጂ በቂ ናቸው ሊባሉ አይችሉም። ይህንን ትልቅ ክፍተት ለመሙላት ደግሞ ከማንም በላይ በዚህ በአሜሪካ የምትኖሩ በዚህ ሙያ የተካናችሁ ወንድሞች እና እህቶች ትልቅ የአገልግሎት እድል የበላይ ተቋዳሾች ናችሁ፣ ስለሆነም ከመቼውም በላይ በትጋት ይህንን አገልሎታችሁን በማጠናከር የታቀዱትን እና ከእቅድም በላይ ለመስራት እንድትበረቱ በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለን።

 

እስከ አሁን በቤቱ የጠበቀን ለዚህ ትልቅ አገልግሎትም የጠራን የቅዱሳን አምላክ ብርታቱን ሰጥቶ ከዚህ ትልቅ በረከት እንድንሳተፍ ይርዳን።

 

ይቆየን!