መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ሐዊረ ሕይወት በሀገረ ጀርመን ተካሄደ
ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም.
ከጀርመን ቀጣና ማእከል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጣና ማእከል በአውሮፓ የመጀመሪያውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ከግንቦት 8-10, 2006 በክሩፈልባክህ (Kroeffelbach) በሚገኘው የኮፕቲክ
ቅዱስ እንጦንስ ገዳም (Sankt-Antonius Kloster) በደማቅ ሁኔታ አካሄደ።
በዚህ ከ80 በላይ ምእመናን በተሳተፉበት መርሐ ግብር ላይ ሰፊ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በተለይ ነገረ ድኅነት እና መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ የተሰጡት ጥልቅ ትምህርቶች ተሳታፊዎች በጉዳዮቹ ላይ የነበራቸውን እውቀት በከፍተኛ ሁኔታ ያሳደጉ እና ታዳሚው ሐዊረ ሕይወት በቅርቡ ይደገምልን የሚል ጥያቄን እንዲሰነዝር ያነሳሱ ነበሩ። በተጨማሪም መዝሙራት በዘማርያንና በሕብረት የቀረቡ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን በሀገር ቤት ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋትበተለይም በተመረጡ ጠረፍና ገጠር አብያተ ክርስቲያናት ላይ አቅዶ እያከናወነው ስላለው የስብከት ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ገለጻ ተደርጓል።
ሐዊረ ሕይወት(አዳማ ማዕከል)
“የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ. . . ይጠቅማል” 2ኛ ጢሞ.3፤16-17
ግንቦት 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖአምላክ
አሰግድመኝ ቅድስት ማርያም ገዳም
ግንቦት 11 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ የ2006 ዓ.ም. ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ተጀመረ
ግንቦት 6 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ለአብነት መምህራንንና ተማሪዎች የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ
በጠረፋማ አካባቢዎች ለተጠመቁ ወገኖች አብያተ ክርስቲያናት ለማነጽ ጥረት እየተደረገ ነው
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በጂንካ፤በግልገል በለስ፤ በቦረና /ተልተሌ/፤ በቦንጋ/ጮራ/ እንዲሁም በሌሎች ጠረፋማ ወረዳዎች ነዋሪዎች ጥምቀት ተከናውኖላቸው የነበረ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ሳይሠራላቸው ቆይቷል፡፡ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራምም ይህንን ችግር ለመፍታት ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ ቤተ ክርስቲያን በማጣት ከአገልግሎት ርቀው ወደ ኢ-አማኒነት እንዳይመለሱ ምእመናን እገዛ ማድረግ እንደሚገባቸው የጠቀሰው የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያው በቅርቡ ሊሠሩ ለታቀዱ ለ12 አብያተ ክርስሰቲያናት የግንባታ ግብአቶችን፤ በተለይም ቆርቆሮ፤ ምስማር፤ እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶችን ምእመናን እንዲረዱ የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጊያ መርሐ ግብር በማኅበሩ ጽ/ቤት አዘጋጅቷል፡፡
“ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፡፡” ሮሜ 6፡5
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
በጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ አሳሳችነት አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔርን ሕግ በመተላላፋቸው ሞተ ሥጋና ሞተ ነፍስ ተፈርዶባቸው ነበር፡፡ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምና ሔዋን ከክህደት የደረሱት በዲያቢሎስ አሳሳችነት በመሆኑና ለሰው ልጆች ካለው ፍጹም ፍቅር የተነሳ የተፈረደባቸውን ሞት በሞቱ ሊደመስስ ሰው ሆነ፡፡ ዮሐ1፡1 ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ 30 ዓመት ሲሞላው ተጠመቀ፡፡ እንደተጠመቀም ልዋል ልደር ሳይል ገዳመ ቆሮንቶስ ሄደ፡፡ በዚያም ጾመ ጸለየ በዲያቢሎስም ተፈተነ፡፡ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ካስተማረ በኋላ አስቀድሞ ለአዳምና ለሔዋን ሞታቸውን ሊደመስስ፡፡ ዕዳቸውን ደመስሶ ነጻ ሊያደርጋቸው በገባው ቃል ኪዳን መሠረት መከራ ተቀበለ፤ በአይሁድ ሸንጎ ፊት ቆመ፣ ምራቅ ተተፋበት፣ ተገረፈ፣ በገመድ ታስሮ ተጎተተ፣ በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ የአዳምና የሔዋንን ዕዳ በደል ደመሰሰ፡፡ ሞት ድል ተነሳ፡፡ ማቴ. 27-28
ማኅበረ ቅዱሳን በሬድዮ አገልግሎቱ የሞገድና ሰዓት ለውጥ አደረገ
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን ድምጸ ተዋሕዶ የተሰኘውንና ዘወትር ዓርብ ከምሽቱ 3፡30 እስከ 4፡30 በአጭር ሞገድ 9850 kHz 19 ሜትር ባንድ ሲሰጠው በነበረው ሳምንታዊ የሬድዮ አገልግሎት ላይ የሥርጭት ሞገድና ሰዓት ለውጥ ማድረጉን አሳወቀ፡፡ ለውጡን ለማድረግ ያስፈለገበትን ምክንያት ዲ/ን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ የማኅበሩ ሚድያ ዋና ክፍል ሓላፊ ሲያስረዱ «ቀድሞ መርሐ ግብሩ ይተላለፍበት የነበረው ሰዓት፤ ዘወትር ዓርብ ከምሽቱ 3፡30 እስከ 4፡30፤ በንጽጽር ምሽት ስለነበር በተለይ በክልል የሚገኙ አድማጮቻችን አገልግሎቱን አለማግኘታቸውን በልዩ ልዩ መንገድ ሲገልጹልን ቆይተዋል፡፡
የማኅበራችን አገልግሎት የክርስቲያናዊ ግዴታችን አካል ነው
ሚያዚያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም.
ክርስቲያኖች የተጠሩት በክርስቶስ እንዲያምኑ በስሙም እንዲጠመቁ ብቻ አይደለም፤ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው የፍቅርና የርኅራኄ ሥራ ለሰዎች ሁሉ እንዲሠሩም ነው፡፡ “ስለ እርሱ መከራ ደግሞ ልትቀበሉ እንጂ በእርሱ ልታምኑ ብቻ አይደለም” /ፊል 1÷29/ ያለው የሐዋርያው ቃሉ ይሄንን ያመለክተናል፡፡ ይኸውም የመንፈስ ፍሬዎችን ይዘን እንድንገኝ የታዘዝንበት ነው፡፡ /ገላ 5÷22/