መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ማኅበረ ቅዱሳን የአልባሳት ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ
ታኅሣሥ 18 ቀን 2006 ዓ.ም.
በታመነ ተ/ዮሐንስ
ያመኑትም ሕዝብ አንድ ልብ አንዲትም ነፍስ ነበሩአቸው
ትኅሣሥ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
አባላቱ አንድ የማኅበረ ቅዱሳን አገልጋይ በተከራየላቸው መለስተኛ አውቶብስ (ሃይገር ባስ) በመሳፈር ከ45 ደቂቃ ጉዞ በኋላ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ላይ የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር ደረስን፡፡ በማኅበሩ አባላት በመሠራት ላይ የሚገኘውን የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እየተሳለምንና በነፋሻማው አየር እየታገዝን ወደ ውስጥ ዘለቅን፡፡ ግቢው በተለያዩ አጸዶች ተውቧል፡፡ ነፍስ ምግቧን ታገኝ ዘንድ ትክክለኛው ሥፍራ በመሆኑ የነፍሳችንን ረሃብ ለማስታገሥ ቸኩለናል፡፡ የአባቶችን ቡራኬ ተቀብለን አጭር የግል ጸሎታችንን አድርሰን ለጉብኝቱ ተዘጋጀን፡፡ ጉብኝቱ የተጀመረው ስለ ጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር አመሠራረት ዲያቆን ደቅስዮስ ገለጻ በማድረግ ነበር፡፡
ግብረ ፊልጶስ ሲምፖዚየም ተካሄደ
ታኅሣሥ 16 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ መርሐ ግብር “ግብረ ፊልጶስ” የተሰኘ ሲምፖዚየም ታኅሣሥ 12 እና 13 ቀን 2006 ዓ.ም. በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ አካሄደ፡፡
የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ደብረ መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን
ታኅሣሥ 9 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ሪፖርታዥ፡-
ከዋዜማው ጀምሮ መርሐ ግብሩን የተሳካ ለማድረግ የማኅበሩ ሐዊረ ሕይወት አዘጋጅ ኮሚቴ በሚመድበው መሠረት የየክፍሉ አገልጋዮች በአገልግሎት ተጠምደዋል፡፡ መርሐ ግብሩን የተሳካ ለማድረግ ሁሉም ይጣደፋል፤ የጎደለውን ይሞላል. . . ፡፡
ከሌሊቱ 12፡00 ጀምሮ አምስት ኪሎ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ከሚገኘው ከማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ ጀምሮ በተለምዶ ሰባ ደረጃ እስከሚባለው ሠፈር ድረስ ሰባ 1ኛ ደረጃ የሚሆኑ የከፍተኛ አገር አቋራጭ አውቶቡሶች መስመራቸውን ይዘው ተሰልፈው የምእመናንን መምጣት ይጠባበቃሉ፡፡
የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በድምቀት ተካሔደ
ማኅበረ ቅዱሳን ለ5ኛ ጊዜ ያዘጋጀውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ደብረ ዘይት በሚገኘው ደብረ መድኃኒት ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ታኅሳስ 6 ቀን 2006 ዓ.ም. ከ 5000 ምዕመናን በላይ በተገኙበት አካሔደ፡፡ ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን፡፡
“ግብረ ፊልጶስ” የተሠኘ ሲምፖዚየም እንደሚዘጋጅ ተገለጸ
ታኅሣሥ 05 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
“ግብረ ፊልጶስ – ሐዋርያዊ ጉዞ በኢትዮጵያ በቀድሞው፤ በመካከለኛውና በአሁኑ ዘመን” በሚል መንፈሳዊ ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ አማካይነት ሲምፖዚየም እንደሚዘጋጅ ተገለጸ፡፡
ተኅሣሥ 12 እና 13 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በሚካሔደው ሲምፖዚየም ላይ ከዚህ በፊት በተልተሌ፤ ጂንካ፤ ከረዩ፤ መተከልና ግልገል በለስ አካባቢዎች ተጠምቀው የእግዚአብሔር ልጅነትን ያገኙ ምእመናን በአካል በመገኘት በጉባኤው ላይ አሁን ያሉበትን ሁኔታ ያቀርባሉ፡፡
የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ ቅርስነት ተመዘገበ
ኅዳር 26 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የኢትዮጵያ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን የኢትዮጵያ የመሰቀል በዓል አከባበር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰሱ ቅርሶች (Intangible) በቅርስነት መመዝገቡን አስመልከቶ ኅዳር 26 ቀን 2006 ዓ.ም. በባለሥልጣኑ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ፡፡
የመስቀል በዓል በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ
የኢትያጵያ የመስቀል ክብረ በዓል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን UNESCO /ዩኔስኮ/ አስታወቀ፡፡ ዝርዝሩን እንደደረስን እናቀርባለን፡፡
ሐዊረ ሕይወት (የሕይወት ጉዞ)
ማኅበረ ቅዱሳን ከስደት ተመላሾችን ለመደገፍ እንደሚሠራ አስታወቀ
ኅዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ከሳውዲ አረቢያ ተመላሽ ወገኖቻችንን ለመደገፍ ቀጣይ ሥራዎችን እንደሚሠራ አስታወቀ፡፡