መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የባሕር ዳር ማእከል ሐዊረ ሕይወት( የሕይወት ጉዞ) ማዘጋጀቱን አስታወቀ
መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
ግዛቸው መንግስቱ ከባሕር ዳር ማእከል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል ምእመናን በጾሙ ወቅት መንፈሳዊ በረከትና ዕውቀት እንዲያገኙ በማሰብ መጋቢት 21/2006 ዓ.ም ወደ ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ አብችክሊ ጽርሐ ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሐዊረ ሕይወት ቁጥር ፪ ማዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡ እንደ ማእከሉ ገለጻ የዚህ የሐዊረ ሕይወት መዘጋጀት ዋና ዓለማው ሕዝበ ክርስቲያኑ በመንፈሳዊ ሕይወቱ እንዲበረታና መንፈሳዊ እድገት እንዲያመጣ ማድረግ ነው፡፡ ዓላማውን ውጤታማ ለማድረግ በዕለቱ ጸሎተ ወንጌል በካህናት ይደረሳል፣ ምክረ አበውና ቡራኬ በሊቃነ ጳጳሳትና ገዳማውያን አባቶች ይሰጣል፣ የተጠየቁ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች በሊቃውንቱ ምላሽ ያገኛሉ፣ ትምርህርተ ወንጌል፣ መዝሙር፣ መነባንቦችና ሌሎችም መንሳፈዊ መርሐ ግብራት በተያዘላቸው መርሐ ግብራት ይቀርባሉ፡፡
የዱባይ ሻርጃ አጅማን ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን 20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ተከበረ፡፡
መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
እርቅይሁን በላይነህ
በሊባኖስ የተባበሩት ዐረብ ኢምሬትና አካባቢው ክብረ በዓሉ የተካሄደው በዱባይ ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳ ላይ በተጣለ ድንኳን ሲሆን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ በበዓሉ ታድመዋል፡፡
ሐዊረ ሕይወት
ሦስተኛው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የጥናት መጽሔት ለኅትመት በቃ
መጋቢት 8 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
የምርምር መጽሔቱ ጠቀሜታ ከፍተኛ እንደሆነ የገለጹት የጥናትና ምርምር ማእከሉ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ስይፈ አበበ “ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች ግብአት ይሆናል፤ቤተ ክርስቲያን በጥናት እና ምርምር የተደገፈ ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት እንድታበረክት ያግዛታል፤ለተለያዩ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ ይሰጣል፤ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት እና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚገኙ ምሁራን ልጆቿን ለቀጣይ ጥናት ያነሳሳል፣ ያበረታታል” ብለዋል፡፡
ጥንታዊቷ የወይብላ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተመዘበረች
መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም.
ሹመት ገ/እግዚአብሔር
በደሴ ማእከል ከወረኢሉ ወረዳ ማእከል
በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን በወረኢሉ ወረዳ የምትገኘው የወይብላ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች ተመዘበረች፡፡
የወይብላ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከወረኢሉ ከተማ 24 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን፤ የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም በግምት ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች ንዋየ ቅድሳቷ የመዘረፍና የመውደም አደጋ ደርሶባታል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ሥርጭት አንደኛ ዓመት ተከበረ
መጋቢት 2 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ሥርጭት አንደኛ ዓመት በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ ባለሀብቶች፣ አርቲስቶች የማኅበሩ ደጋፊዎችና የማኅበሩ የሥራ አመራር አባላት በተገኙበት ተከበረ፡፡
በዕለቱ የቴሌቭዥን ሥርጭቱን አንደኛ ዓመት ለማክበር የተገኙትን ባለድርሻ አካላት “እንኳን ደኅና መጣችሁ” ያሉት የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሰሙ ምትኩ እንደገለጹት “ማኅበረ ቅዱሳን ወንጌለ መንግሥትን ለዓለም ለማዳረስ በሚደረገው መንፈሳዊ አገልግሎት የኅትመት ውጤቶች ሲጠቀም መቆየቱን ገልጸው አሁንም በቴክኖሎጂው በመታገዝ በዓለም ሁሉ ከምንደርስበት መንገዶች አንዱ የቴሌቪዥን መርሐ ግብሩ መጀመር የምሥራች ሲሆን በእውቀት፣ በገንዘብ፣ በጉልበት ድጋፋችሁ ሁል ጊዜ የማይለየን ክቡራን እንግዶቻችን አሁንም ድጋፋችሁ እንዳይለየን በሚል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የደሴ ማእከል ቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል ስለቤተክርስቲያን ዘላቂ ልማት ከበጎ አድራጊዎች ጋር ውይይት አደረገ፡፡
የካቲት 28 ቀን 2006 ዓ.ም.
ወርቁ በላይሁን ደሴ ማእከል
የደሴ ማእከል ቅዱሳት መካናትና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል “ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት በጋራ እንሥራ” በሚል መርህ ለሁለተኛ ጊዜ ከደሴ ከተማ በጎ አድራጊዎች ጋር የካቲት 23 ቀን 2006 ዓ.ም ውይይት አደረገ፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ
ጥሪ የተደረገላቸው በጎ አድራጊዎች የተገኙ ሲሆን፤ ለዘላቂ የቤተ ክርስቲያን ልማት መሠራት ስለሚገባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውይይት ተደርጓል፡፡
ምኲራብ
የካቲት 27 ቀን 2006 ዓ.ም.
ታመነ ተ/ዮሐንስ
“ዘወትርም በቤተ መቅደስ ያስተምር ነበር” ሉቃ.19፥47
ምኲራብ የአይሁድ የጸሎት ቤት ሲሆን በብሉይ ኪዳን ዘመን የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተ መቅደስና በሥርዓቱ የተመሠረተ ነበር፡፡ ናቡከደነጾር ግን ቤተ መቅደሱን አፈረሰ ሕዝቡንም ወደባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚያም ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማኅበረተኛነት ልዩ ቤት ሊሠሩ እንደጀመሩ ይታሰባል፡፡ /የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት/
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በዓለ ሢመት ተከበረ::
የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርእስ ጥናት አቀረበ
የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርዕስ በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ዋና ክፍል አዘጋጅነት በአቶ አለማ ሐጎስ አቅራቢነትና በአቶ አበባው አያሌው አወያይነት በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም ቀረበ፡፡