senbt 2006 2

የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ተጠናቀቀ

 ሰኔ 2 ቀን 2006 ዓ.ም.

senbt 2006 2ከግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ቀናት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲካሔድ የቆየው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 3ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡

senbt 2006 3ጉባኤው በመጨረሻ ቀን ውሎው በየአኅጉረ ስብከቱ የሚታዩ እንቅስቃሴዎችንና ችግሮች አስመልክቶ ተሳታፊዎቹ በቡድን ውይይት በማድረግ ለጉባኤው አቅርበዋል፡፡ የግጭት አፈታት ዘዴን አስመልክቶ በመምህር በለጠ ብርሃኑ ጥናታዊ ጽሑፍ የቀረበ ሲሆን፤ በቀጣይ አንድ ዓመት ተፈጻሚ የሚሆኑ እቅዶች ላይ ውይይት ተካሒዶባቸዋል፡፡

በጉባኤው ማጠናቀቂያ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ሓላፊ የስልጤ፤ ጉራጌና ሃዲያ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለሁለት ቀናት በጉባኤው ለተገኙና ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን ትብብር ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የወላይታ ኮንታና ዳውሮ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምእዳን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ውስጥ በርካታ ችግሮች እንዳሉ በመግለጽ፤ በቅድሚያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ራሳቸውን መመልከት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ ሁሉም የየራሱን ድርሻ ከተወጣ አሁን እየታዩ ያሉ ችግሮች እንደሚወገዱ በመጠቆም ጠንክሮ መሥራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡

 senbt 2006 1

senbt 2006 4