meglecha 2006 01

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የግንቦቱ ርክበ ካህናት መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ

ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ.ም.

  • በቅዱስ ሲኖዶስ የቀረበው መግለጫ ውሳኔ ያላገኙ አጀንዳዎችን አካቷል

meglecha 2006 01ከግንቦት 6 ቀን 2006 ዓ. ም. ጀምሮ ሲካሔድ የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ. ም. መግለጫ በመስጠት ተጠናቋል፡፡ ጉባኤው ሲጠናቀቅ በቀረበው መግለጫም ውሳኔ ሳያገኙ የቀሩ አጀንዳዎችን አካቷል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፡-

  • የብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቅዱስ ፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ፤ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ረዳት ሊቀ ጳጳስነት ተነስተው የጅማ ሀገረ ስበከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲሠሩ ሲወሰን፤ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሳይመደብለት ታልፏል፡፡

  • የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ 34 ገጽ ለጉባኤው ቀርቦ ምልዓተ ጉባኤው በስፋት ውይይት ማድረጉን ከመግለጽ ውጪ ውሳኔ ሳይሰጠው ቀርቷል፡፡

ዝርዝሩን ከሙሉ መግለጫው ይከታተሉ፡፡

 meglecha 2006 02