debre libanose

የደብረ ሊባኖስ ገዳምን ለመታደግ ጥሪ ቀረበ

 ሰኔ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

debre libanoseየደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ያጋጠሙትን በርካታ ችግሮች ለመታደግ ዘላቂ መፍትሔ መሻት እንደሚገባ ሰኔ 8 ቀን 2006 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በተካሔደ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ጥሪ ቀረበ፡፡

debre libanose 2006 2ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገዳሙ ያለበትን ችግር አስመልክቶ ሲገልጹ “የደብረ ሊባኖስ ገዳም የኢትዮጵያዊያን ሁሉ ገዳምና ሀብት ነው፡፡ ገዳምነቱን ሊሸረሽሩ የሚችሉ በርካታ ችግሮች አጋጥመውታል፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመፍታትና የአባቶች የጸሎት ቦታ ተጠብቆ እንዲቆይ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ ስለሆነ ምእመናን ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል” ብለዋል፡፡

የገዳሙ አስተዳዳሪ ፀባቴ አባ ወልደ ማርያም አድማሱ የጉዳዩ አሳሳቢነትና ሊወሰድ ስለሚገባው አፋጣኝ መፍትሔ ሲያብራሩ “ገዳሙ ጊዜ የማይሰጥ፤ የቤተ ክርስቲያኑን ሕልውና የሚፈታተኑ በርካታ ችግሮች ከፊት ለፊት ተደቅነውበታል፡፡ ከተራራማው አካባቢ ወደ ታች በሚወርደው ጎርፍ መሬቱ እየተንሸራተተና እየተሰነጠቀ ነው፡፡ የገዳማውያኑና የምእመናን ቦታዎች ያለመለየት፤ ሕገ ወጥ የመሬት ወረራ፤ የገዳሙ ወደ ከተማነት እየተቀየረ መምጣት፤ የአካባቢያዊ ንጽሕና መጓደልና ሌሎችም ችግሮች አሉብን” ሲሉ ገልጸዋል፡፡፡

ገዳሙ ገዳማዊ ሕይወቱን ጠብቆ እንዲዘልቅ በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ጥናት ተካሒዶ፤ ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኙ የሚናገሩት ፀባቴ አባ ወልደ ማርያም፤ በተዘጋጀው ፕሮጀክት መሠረት የመጸዳጃ ቤትና የጎርፍ መከለያdebra libanose 2006 1 ግንባታ በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ያስረዳሉ፡፡ ምእመናን ይህንን በመረዳት የታቀዱት ፕሮጀክቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው እንዲተገበሩም የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ሊተገበሩ የታቀዱት 11 ፕሮጀክቶች መሆናቸውን በመጥቀስ ለጉባኤው በዝርዝር ያቀረቡት ኢንጂነር ዮናስ ምናሉ እስካሁን ድረስ ኣፋጣኝ እርምጃ ባለመወሰዱም በጎርፍ ዐራቱ ተግባር ቤቶች፤ የመናንያኑ መኖሪያዎች፤ እንዲሁም ድልድዩ ጉዳት እንደደረሰባቸውና፤ የቤተ ክርስቲያኑንም መሠረት እየቦረቦረው እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ተገኝተው የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን፤ ምእመናን የድጋፍ ማድረጊያ ቅጽ እንዲሞሉ ተደርጓል፤ ጨረታም ተካሒዷል፡፡ ይህ ጉባኤ የመጀመሪያ መሆኑንና በቀጣይነት የሚካሄዱ የገቢ ማሰባሰቢያና ሌሎች ዝግጅቶች እንደሚኖሩም ተጠቅሷል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን መዝሙር ክፍል አባላትና የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ዝማሬ፤ እንዲሁም በገጣሚያን ግጥም ቀርቧል፡፡