መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
፲ቱ ማዕረጋት
ሐምሌ 14 ቀን 2006 ዓ.ም.
መምህር ደጉ ዓለም
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ
የሐዲስ ኪዳን መምህር
ቅዱሳን ማለት የተቀደሱ፣ የከበሩ፣ የተመሰገኑ፣ የተለዩ፣ የተመረጡ፣ ንጹሐንየሆኑ፣ የጠሩ….. ወዘተ ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን በዚህ ስም የሚጠሩበት ከሰው ወይም ከምድራዊ ባለሥልጣን የተቸሩት አይደለም፡፡
በሃይማኖት ጸንተው በምግባር ጐልምሰው የሥጋ ምኞታቸውን ጥለው አፍርሰው ሲገኙ የቅድስና ባለቤት ቅዱስ እግዚአብሔር እነሱን /ቅዱሳንን/ መሣሪያ አድርጐ ኃይሉንና ሥልጣኑን ቢገልጽባቸው ማኅደረ እግዚአብሔር መሆናቸው ይገለጻል፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱሳን ይባላሉ፡፡ እሱ እግዚአብሐር ቅዱስ ተብሏልና የጌትነቱ መገለጫ የሆኑ ሁሉ ቅዱሳን ይባላሉ ጻድቃን እንደመ ላእክት ውሉደ እግዚአብሔር ይባላሉ /ኢዮ.1፡6/፣ ሮሜ.8፡14/ ቅዱሳን ጻድቃን በግብር መላእክትን መስለው ሆነው የፈጣሪአቸውን ፈቃድ ፈጽመው በመገኘታቸው ከዚህ ዓለም በመለየታቸው ቅዱሳን ሲባሉ የፈጣሪአቸውን ሕያው መንግሥት ወራሾች ናቸውና ውሉደ እግዚአብሔር ይባላሉ፡፡ በሌላም ቃል ውሉደ ብርሃን ይባላሉ፡፡ /ሉቃ.16፡8/ በዓለማቸው ይራቀቃሉና ይህን ዓለም ይጠሉታል፡፡ ውሉደ ሕይወት ይባላሉ ሞትንና የሞት ከተማ ይህን ዓለም ይንቃሉና በክብር ተነሥተው ዳግመኛ ሲሞቱ የማይገባቸው ስለሆነ /ሉቃ.10፡30/ ውሉደ ጥምቀት ተብለዋል ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትናን ተጐናጽፈዋልና፡፡ ውሉደ መንግሥትም ተብለዋል የመንግሥተ ሰማያት ባለቤቶች ናቸውና፡፡ በጸጋ እግዚአብሔር የበለጸጉ በመሆናቸው የእግዚአብሔር አዕይንተ እግዚአብሔር ተብለዋል /መዝ.33፡15/
የጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን
ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
ክፍል አንድ፡-
በጎንደር ከተማ በርካታ ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ሲሆን አብያተ ክርስቲያናቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ደንብ ጠብቀው፣ እንዲሁም በዘመኑ የነበሩ የኢትዮጵያዊያን የሥልጣኔ ደረጃ ከፍተኛ መሆንን የሚያመለክቱ አሻራዎች አርፎውባቸዋል፡፡ ይህንንም አሻራዎቻቸውን ይዘው ዛሬ ድረስ ዓለምን እያስደመሙ ይገኛሉ፡፡ እነዚህም አድባራትና ገዳማት በነገሥታት፤ በባላባቶችና በሀገሬው ሰው የተተከሉ ሲሆኑ፤ በነገሥታቱ ከተተከሉት አድባራት ውስጥ በ1703 ዓ.ም በንጉሡ በዐፄ ዮስጦስ የተመሠረተችው የጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አንዷ ናት፡፡
ማቴዎስ ወንጌል
ሐምሌ 9 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ አምስት
የተራራው ስብከት /አንቀጸ ብፁዓን/
ይህ ምዕራፍ ልዑለ ባሕርይ አምላክ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ተራራ ወጥቶ ከፍ ካለ ቦታ ተቀምጦ ያስተማረው ትምህርት በመሆኑ የተራራው ስብከት በመባል ይታወቃል፡፡ ብፁዓን እያለ በማስተማሩም አንቀጸ ብፁዓን ይባላል፡፡ ጌታችን ከፍ ካለ ቦታ ተቀምጦ ያስተማረበት ምክንያት፣ መምህር ከፍ ካለ ቦታ ተማሪዎች ደግሞ ዝቅ ካለ ቦታ ተቀምጠው የሚማሩት ትምህርት ስለሚገባ ነው፡፡
በዓለ ሥላሴ
ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
ወበዛቲ ዕለት ቦኡ ሥሉስ ቅዱስ ውስተ ቤተ አብርሃም ወተሴሰዩ ዘአቅረቦ ሎሙ፡፡ በከመ መጽሐፍ ውስተ ኦሪት ወአብሠርዎ ልደቶ ለይስሐቅ ወባረክዎ፡፡ በዚችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት /ቅድስት ሥላሴ/ በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገቡ፡፡ የይስሐቅንም ልደት አበሠሩት ባረኩት አከበሩትም፡፡
መጽሐፈ ስንክሳር ዘሐምሌ ሰባት
ሥላሴ ማለት በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት አንድ አምላክ በሦስት አካላት እንዳለ ለአበው ለነቢያትና ለሐዋርያት መገለጡን አምነን የምንማረው ትምህርት ነው፡፡ሥላሴ ማለት የግእዝ ቃል ሲሆን ሦስት፤ ሦስትነት ማለት ነው፡፡
“ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ፤ ስለ መንግሥተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ፡፡” ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ቁ.6
ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም በቅዱስ ዳዊት ሕይወት የተከወናውን በምሥጢር ስቦ አምጥቶ የሰማዕታትን ክብር አጎልቶ ተናግሮበታል፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊትን እግዚአብሔር አምላክ ለእስራኤል አነገሠው፡፡ በዙሪያው የነበሩ ኤሎፍላዊያንን አጥፍቶ ደብረ ጽዮንን /መናገሻ ከተማውን/ አቅንቶ ሲኖር ከዕለታት አንድ ቀን ዳዊት ታመመ፡፡የዳዊትን መታመም ሰምተው፣ ካሉበት ተነስተው የዳዊትን ከተማ በተለይም ቤተልሔምን ከበቧት፡፡ ዳዊት ይህን ሰምቶ “ወይ እኔ ዳዊት! ድሮ ታመምሁና ጠላቶቼ ሰለጠኑ ሲል የኀያላኑን ልቦና ለመፈተን ከቤተልሔም ምንጭ ውኃ ማን ባመጣልኝ?” አለ፡፡ በዚህ ጊዜ የጭፍሮቹ አለቆች ሦስቱ ማለትም አዲኖን፣ ኢያቡስቴ ኤልያና ረዋታቸውን /የውኃ መያዣ/ ይዘው፣ ጦራቸውን አሰልፈው፣ ጠላቶቹን ድል ነስተው፣ ዳዊት ሊጠጣ የወደደውን ውኃ አመጡለት፡፡ቅዱስ ዳዊትም ያንን ውኃ አፈሰሰው “ለምን አፈሰስከው?” ቢሉት “ደማችሁን መጣጠት አይደለምን?” ብሎ፤ ይህም ከጽድቅ ገብቶ ተቆጠረለት፡፡ 2ሳሙ.23፥13-17
የማቴዎስ ወንጌል
ሐምሌ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ አራት
በዚህ ምዕራፍ መጀመሪያ ያለው ንባብ የሚተርክልን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር በኢያሪኮ አካባቢ ወደሚገኘው /ሣራንደርዮን/ የአርባ ቀን ተራራ ተብሎ ወደሚታወቀው ሥፍራ ወጣ፡፡ በዚያም ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት ጾመ፣ ከዚህ በኋላ ተራበ፤ ጸላኤ ሠናይት ዲያብሎስ ሦስት ፈተናዎችን አቀረበለት፡፡
የንባብ ባህልን ለማሳደግ ቤተ ክርስቲያን የሚኖራት ድርሻ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም.
ይብረሁ ይጥና
ሠኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ለግማሽ ቀን በማኅበሩ ሕንፃ ላይ በተካሔደው ጉባኤ ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል በዕውቀት እና በሥነ ምግባር የታነፀ ዜጋ ለማፍራት በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን፤ “የንባብ ባሕልን ለማሳደግ የተለያዩ አካላት ሚና” ፤ እንዲሁም “ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በሚሉ ሁለት ርእሰ ጉዳች ላይ የተደረጉ ጥናቶች ቀርበዋል፡፡
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርትን አስመረቀ
ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
ዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
ሰኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት “የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እምነቷን፤ ትውፊቷንና ታሪኳን እንደተጠበቀ ለትውልዱ ሁሉ እንድታደርሱላት አደራ ተረክባችኋል” ብለዋል፡፡
ዐውደ ርዕዩ ተጠናቀቀ
ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
አውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል
በሀገረ ጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ ለሦስት ቀናት ለሕዝብ ክፍት ሆኖ የቆየው ዐውደ ርዕይ ተጠናቀቀ፡፡
“ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል ርዕስ ተዘጋጅቶ ሲታይ የሰነበተው ዐውደ ርእይ በፍራንክፈርትና አካባቢው በሚኖሩ በርካታ ምእመናን ተጎብኝቷል፡፡ ዐውደ ርእዩን የጎበኙ ምእመናንም ባዩት ነገር እንደተደሰቱና ብዙ ትምህርት እንዳገኙበት ገልጸዋል፡፡
“ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” ዐውደ ርዕይ ተከፈተ
ሰኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም.
አውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል በፍራንክፈርት ከተማ ኢኮነን ሙዚየም ያዘጋጀው ዐውደ ርእይ ተከፈተ፡፡
ከሰኔ 27- 29 ቀን 2006 ዓ.ም./July 4-6, 2014/ እንዲታይ የተዘጋጀው ዐውደ ርእይ ጥሪ የተደረገላቸው ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከፍቷል፡፡ ጸሎተ ወንጌል በቦታው በተገኙ ካህናት ተደርጓል፤ የዐውደ ርእዩን የዝግጅት ሒደትና ይዘት አስመልክቶም አቶ ቃለ አብ ታደሰ የዝግጅት ኮሚቴው ሰብሳቢ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡