መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ማቴዎስ ወንጌል
ሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ 7 ካለፈው የቀጠለ
ሠ. ሰፊ ደጅ የተባለች ባለጸጋን መጽውት ድኃን ጹም ማለት ነው፡፡
ሰፊ ደጅ የተባለች ፈቃደ ሥጋ ናት ወደ ሰፊው ደጅ የሚገቡ ብዙዎች ወደ ጠባቧ ደጅ የሚገቡ ደግሞ ጥቂቶች መሆናቸው ጌታን አያስቀናውም፡፡ ምክንያቱም ጥቂት ዕንቁ ያለው ደግሞ ብዙ ወርቅ ባለው፤ ጥቂት ወርቅ ያለው ብዙ ብር ባለው፤ ጥቂት ብር ያለው ብዙ ብረት ባለው፤ ጥቂት ብረት ያለው ብዙ ሸክላ ባለው አይቀናም፡፡
የ2006 ዓ.ም. የግቢ ጉባኤያት ፍሬዎች ዋንጫና ሜዳልያቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን አስረከቡ
ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም
እንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሔደ
ነሐሴ 27 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
ማቴዎስ ወንጌል
ነሐሴ 22 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ 7
በማቴዎስ ወንጌል በምዕራፍ ሰባት ውስጥ የሰውን ነውር ከማጋነን ይልቅ የራስን ባሕርይ መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን በሰፊው እንማራለን፡፡ ዋና ዋና አሳቦቹም የሚከተሉት ናቸው፡፡
ስለ ፍርድ
የተቀደሰውን ለውሾች መስጠት እንደማይገባ
ዕንቁን በእሪያዎች ፊት ማስቀመጥ እንደማይገባ
ስለ ልመና
ስለ ጠባቧ ደጅ እና ስለ ሰፊው ደጅ
ስለ ሐሰተኞች ነቢያት
በዐለት ላይ ስለተመሠረተውና በአሸዋ ላይ ስለተመሠረተው ቤት
በግሪክ አቴንስ ዐውደ ርእይ ተካሔደ
ነሐሴ 19 ቀን 2006 ዓ.ም.
አውሮፓ ማእከል
የግእዝ ሥርዓተ ንባብ (pronounciation)
ነሐሴ 19 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር
የግእዝ ሥርዓተ ንባብ ስምንት ናቸው፡፡ እነርሱም፡-
ማንሳት 5. ማናበብ
መጣል 6. አለማናበብ
ማጥበቅ 7. መዋጥ
ማላላት 8. መቁጠር ናቸው፡፡
“አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት” /መዝ.131፥8/
ነሐሴ 14 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
ማኅበረ ቅዱሳን በጀርመን ዐውደ ርእይ አካሔደ።
ነሐሴ 14 ቀን 2006 ዓ.ም.
በጀርመን ቀጠና ማእክል
አድርሺኝ
ነሐሴ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
የማቴዎስ ወንጌል
ነሐሴ 9 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ ስድስት
በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የሚከተሉት አሳቦች ተጠቃልለው ይገኛሉ፡፡
የምጽዋት ሥርዓት
ጠቅላላ የጸሎት ሥርዓት
የአባታችን ሆይ ጸሎት
ስለ ይቅርታ
የጾም ሥርዓት
ስለ ሰማያዊ መዝገብ
የሰውነት መብራት
ስለ ሁለት ጌቶች
የዕለት ጉርስና የዓመት ልብስ
1. የምጽዋት ሥርዓት፡- ጌታችን በዚህ ትምህርቱ እንደ ግብዞች መመጽወት እንደማይገባ ተናግሯል፡፡ ግብዞች የሚመጸውቱት ሰው ሰብስበው፣ ቀን ቀጥረው በተመሳቀለ ጉዳና በአደባባይ ነው፡፡ የሚመጸዉቱትም ለመጽደቅ ሳይሆን ለውዳሴ ከንቱ ስለሆነ፤ ስለዚህም አንተ በምትመጸውትበት ጊዜ ቀኝ እጅህ የምትሠራውን ግራ እጅህ አትወቀው ብሏል፡፡ እንዲህም ያለበት ምክንያት፡-