ge awd 2006 44

ዐውደ ርዕዩ ተጠናቀቀ

ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.

አውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል

በሀገረ ጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ ለሦስት ቀናት ለሕዝብ ክፍት ሆኖ የቆየው ዐውደ ርዕይ ተጠናቀቀ፡፡

ge awd 2006 44
“ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል ርዕስ ተዘጋጅቶ ሲታይ የሰነበተው ዐውደ ርእይ በፍራንክፈርትና አካባቢው በሚኖሩ በርካታ ምእመናን ተጎብኝቷል፡፡ ዐውደ ርእዩን የጎበኙ ምእመናንም ባዩት ነገር እንደተደሰቱና ብዙ ትምህርት እንዳገኙበት ገልጸዋል፡፡

ዝግጅቱ በልዩ ልዩ የጀርመንና የአውሮፓ ከተሞች ቢደረግ ምእመናን ስለ ቤተ ክርስቲያናቸውና እምነታቸው በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ ስለሚረዳቸው በተከታታይ እንዲቀርብ የዐውደ ርዕዩ ተሳታፊዎቹ ለኮሚቴው የአደራ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ከዐውደ ርዕዩ ጎን ለጎንም ሰፊ የስብከተ ወንጌልና የምክር አገልግሎት ከኢትዮጵያ በመጡ መምህራን ሲሰጥ ሰንብቷል፡፡

በአጠቃላይ ዐውደ ርዕዩ እንደታሰበው የተከናወነና ውጤታማ እንደነበር ዐውደ ርእዩን ያዘጋጀው በማኅበረ ቅዱሳን የጀርመን ቀጠና ማእከል አባላት ገልጸዋል፡፡