mkgermany exhibition 2

ልዩ ዐውደ ርዕይ በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ ይካሔዳል

ሰኔ 25 ቀን 2006 ዓ.ም.

አውሮፓ ማእከል

mkgermany exhibition 2በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል “ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል መሪ ቃል ልዩ ዐውደ ርዕይ፤ ዐውደ ጥናትና የስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር በፍራንክፈርት ከተማ ኢኮነን ሙዚየም ከሰኔ 27- 29 ቀን 2006 ዓ.ም./July 4-6, 2014/ እንደሚካሔድ ቀጠና ማእከሉ አስታወቀ፡፡

በዝግጅቱም የኢትዮጵያ ጥንታዊ ገዳማትና አብነት ትምህርት ቤቶች ታሪክ አስተዋጽኦና ወቅታዊ ሁኔታ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ እንቅስቃሴ በጀርመንና በአውሮፓ፤ የቅዱስ ያሬድ አጠቃላይ የዜማ ባሕል እና ሌሎችም ጥናታዊ ጽሑፎች ይቀርባሉ፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ በአውሮፓ ሀገራት የሚገኙ የማኅበሩ አባላትና ምእመናን ታዳሚ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡