መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ቅዱስ ፓትርያርኩ ጾመ ፍለሰታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ
ሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም.
ዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ 16 የሚጾመው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጾም ዘንድሮም የፊታችን ሐሙስ ይጀምራል፡፡
ከጠረፋማ አካባቢዎችና ከግቢ ጉባኤያት ለተውጣጡ ተተኪ መምህራን ሥልጠና እየተሰጠ ነው
ሐምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
የአውሮፓ ማእከል ጠቅላላ ጉባኤ ተደረገ
ሐምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
በአውሮፓ ማእከል ሚድያና ቴክኖሎጂ ክፍል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ከሐምሌ 11 እስከ 14 ቀን 2006 ዓ.ም. በኢጣልያ ዋና ማእከል ሮሜ ማእከል አካሄደ፡፡
“መላእክት ሁሉ ረቂቃን አይደሉምን የዘላለም ሕይወትን ይወርሱ ዘንድ ላላቸው ለአገልግሎት ይላኩ የለምን” ዕብ.1፡14
ሐምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
መላእክት እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን የሰማይንም ሠራዊት ፈጠረ በሚለው አንቀጽ እንደተጠቀሰው፤በመጀመሪያው ቀን በዕለተ እሑድ በእግዚአብሔር ቃል ተፈጥረዋል፡፡ እግዚአብሔር አፈጣጠሩ ድንቅ ነውና መላእክትን እንደ እሳትና ነፋስ የማይዳሰሱ የማይታዩ አድርጎ ፈጥሯቸው ያመሰግኑታል፡፡ ዘፍ.1፡1 መዝ.108፡4፣ ዕብ.1፡12
እግዚአብሔር የፈጠራቸው 20 ዓለማት ሲኖሩ ሦስቱ፤ ኢዮር፣ ራማ፣ ኤረር የመላእክት ከተሞች ናቸው፡፡
የጎንደር መካነ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን
ሐምሌ 16 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
ክፍል ሁለት
ጥምቀት
በጎንደር ጥምቀትን አስመልክቶ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ጥምቀተ ባሕር የሚወርዱበትና የሚመለሱበት ሦስት ዓይነት ሥርዓት ይገኛሉ፡፡ እነዚህም እየተፈጸሙ እስከ ዛሬ ድረስ ደርሰዋል፡፡
ሊቁ አለቃ ወልደ ሰንበት ተገኝ አረፉ
ሐምሌ 15 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ከ40,000 በላይ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችን አስመረቀ
ሐምሌ 15 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ40,000 በላይ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችን አስመረቀ ፡፡
ክረምት
ሐምሌ 15 ቀን 2006 ዓ.ም.
ካለፈው የቀጠለ
ከሐምሌ 19 እስከ ነሐሴ 21 ቀን ድረስ ያለው መካከለኛ ክረምት በመባል ይታወቃል፡፡ የክረምት ኃይልና ብርታት እንዲሁም ክረምትን ጥግ አድርገው የሚከሰቱ የተፈጥሮ ኃይላት ዑደት ያጸናበታል፡፡\ የዕለቱ ቁጥርም 33 ዕለት ነው፡፡ በዚህ ጊዜ መብረቅ፣ ነጎድጓድ ባሕርና አፍላግ ይሰለጥናሉ፡፡
መብረቅ የአምላክን ፈጣንነት፣ ነጎድጓድ የግርማውን አስፈሪነት፣ ባሕር የምሕረቱን ብዛት የሚያመለክቱ የእግዚአብሔር ባሕርይ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ በዚህ ወቅት ጥልቆቹ የውኃ ቦታዎች መጠናቸው ያድጋል፣ የወንዞች ሙላት ይጨምራል፣ ምንጮች ይመነጫሉ፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም “ዘይመይጦ ለመብረቅ ወያጸንኦ ለነጎድጓድ ዘርዋነ ያስተጋብዕ ወያበርህ ለመሃይምናን” /ድጓ ዘክረምት/ መብረቅን የሚመልሰው፣ ነጎድጓድን የሚያበረታው የተበታተኑትን ይሰበስባል፣ ለሚያምኑባትም ዕውቀትን ያድላል በማለት ብርሃንን ከምዕራብ ወደምሥራቅ እንደሚመልሰው ሁሉ መብረቅንም ካልነበረበት በጋ ወደሚኖርበት ክረምት የሚያመጣውና መገኛውን ደመና የሚፈጥርለት እርሱ ብቻ መሆኑን ያስረዳል፡፡
፲ቱ ማዕረጋት
ሐምሌ 14 ቀን 2006 ዓ.ም.
መምህር ደጉ ዓለም
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ
የሐዲስ ኪዳን መምህር
ቅዱሳን ማለት የተቀደሱ፣ የከበሩ፣ የተመሰገኑ፣ የተለዩ፣ የተመረጡ፣ ንጹሐንየሆኑ፣ የጠሩ….. ወዘተ ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን በዚህ ስም የሚጠሩበት ከሰው ወይም ከምድራዊ ባለሥልጣን የተቸሩት አይደለም፡፡
በሃይማኖት ጸንተው በምግባር ጐልምሰው የሥጋ ምኞታቸውን ጥለው አፍርሰው ሲገኙ የቅድስና ባለቤት ቅዱስ እግዚአብሔር እነሱን /ቅዱሳንን/ መሣሪያ አድርጐ ኃይሉንና ሥልጣኑን ቢገልጽባቸው ማኅደረ እግዚአብሔር መሆናቸው ይገለጻል፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱሳን ይባላሉ፡፡ እሱ እግዚአብሐር ቅዱስ ተብሏልና የጌትነቱ መገለጫ የሆኑ ሁሉ ቅዱሳን ይባላሉ ጻድቃን እንደመ ላእክት ውሉደ እግዚአብሔር ይባላሉ /ኢዮ.1፡6/፣ ሮሜ.8፡14/ ቅዱሳን ጻድቃን በግብር መላእክትን መስለው ሆነው የፈጣሪአቸውን ፈቃድ ፈጽመው በመገኘታቸው ከዚህ ዓለም በመለየታቸው ቅዱሳን ሲባሉ የፈጣሪአቸውን ሕያው መንግሥት ወራሾች ናቸውና ውሉደ እግዚአብሔር ይባላሉ፡፡ በሌላም ቃል ውሉደ ብርሃን ይባላሉ፡፡ /ሉቃ.16፡8/ በዓለማቸው ይራቀቃሉና ይህን ዓለም ይጠሉታል፡፡ ውሉደ ሕይወት ይባላሉ ሞትንና የሞት ከተማ ይህን ዓለም ይንቃሉና በክብር ተነሥተው ዳግመኛ ሲሞቱ የማይገባቸው ስለሆነ /ሉቃ.10፡30/ ውሉደ ጥምቀት ተብለዋል ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትናን ተጐናጽፈዋልና፡፡ ውሉደ መንግሥትም ተብለዋል የመንግሥተ ሰማያት ባለቤቶች ናቸውና፡፡ በጸጋ እግዚአብሔር የበለጸጉ በመሆናቸው የእግዚአብሔር አዕይንተ እግዚአብሔር ተብለዋል /መዝ.33፡15/
የጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን
ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
ክፍል አንድ፡-
በጎንደር ከተማ በርካታ ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ሲሆን አብያተ ክርስቲያናቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ደንብ ጠብቀው፣ እንዲሁም በዘመኑ የነበሩ የኢትዮጵያዊያን የሥልጣኔ ደረጃ ከፍተኛ መሆንን የሚያመለክቱ አሻራዎች አርፎውባቸዋል፡፡ ይህንንም አሻራዎቻቸውን ይዘው ዛሬ ድረስ ዓለምን እያስደመሙ ይገኛሉ፡፡ እነዚህም አድባራትና ገዳማት በነገሥታት፤ በባላባቶችና በሀገሬው ሰው የተተከሉ ሲሆኑ፤ በነገሥታቱ ከተተከሉት አድባራት ውስጥ በ1703 ዓ.ም በንጉሡ በዐፄ ዮስጦስ የተመሠረተችው የጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አንዷ ናት፡፡