hawassa 1a

የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ባለ 4 ፎቅ ሁለገብ ህንጻ እና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት አስመረቀ

 

የካቲት 09ቀን 2007ዓ.ም.

ዲ/ን ያለው ታምራት

hawassa 1aበሲዳማ፣ጌዲኦ.አማሮና ቡርጂ ሀገረ ሰብከት በሐዋሳ ወረዳ ቤተ ክህነት የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አዲስ ያሰገነባውን ባለ 4 ፎቅ ሁለ ገብ ህንጻ እና ት/ቤት ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ፣የክልሉ ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት እና ምዕመናን በተገኙበት የካቲት 7 ቀን 2007 ዓ.ም በድምቀት አስመረቀ፡፡

 

ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የምርቃ መርሐግብሩን በጸሎት ባርከው ከከፈቱ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት “ዛሬ በምንመርቃቸው የልማት ሥራዎች ለቤተ ክርስቲያን እና ለመንግስት ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኙ ከመሆናቸው በተጨማሪ ከፍተኛ የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ” ብለዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አክለውም “ት/ቤቱ በሃይማኖት ሳይለይ የልዩ ልዩ ቤተ እምነት ተከታዮች ልጆች ተቀብሎ በሥነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉ በማድረግ ለሀገር የሚጠቅም ትውልድ አያፈራ ይገኛል” ብለዋል፡፡hawassa2b

 

የዕለቱ የክብር እንግዳ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የንድግና ኢንደስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ እንደገለጹት “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሰላምና ልማትን ከመገንባት አንጻር እያበረከተችው ያለችው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የተገነባው ሁለ ገብ ህንጻ ለሀዋሳ ከተማ ተጨማሪ ውበት ሆኗል” ብለዋል፡፡

 

hawassa3a

የገዳሙ የልማት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ተከስተ ብርሃን ሀጎስ በሪፖርታቸው እንደገለጹት “ይህ ከስድስት ዓመት በፊት ግንቦት 2001 ዓ.ም የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ ዛሬ ለምረቃ የበቃው ሁለገብ ህንጻ 30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚገመት ሲሆን ከገዳሙ ካዝና ወጪ የተደረገው 8 ሚሊየን ብር ብቻ ነው፡፡ ቀረው ወጪ ግን በኮሚቴው አባላትና እና በከተማው በሚገኙ ባለ ሀብት የቤተ ክርስቲያን ልጆች የተሸፈነ እንደ ሆነ” ገልጸዋል፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢ ህንጻው የተሰራበትን ዓላማ ሲገልጹ “ይህን ህንጻ በማከራየት የሚገኘው ገቢ ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት መርጃ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ነው” ብለዋል፡፡

 

በመጨረሻ በገዳሙ የተሠሩት የልማት ሥራዎች ሁለ ገብ ባለ 4 ፎቅ ህንጻ እና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት በተጋዛዥ እንግዶችና ምዕመናን ተጎብኝተዋል፡፡ ከጉብኝቱ በኋላ ያናገርናቸው ምዕመናን እንደገለጹልን የገጠር አብያተ ክርስቲያናን ከመዘጋት አደጋ ለመታደግ በከተማ የሚገኙ አድባራት እንደዚህ አይነት የልማት ሥራ መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡