የ፳፻፯(2007)ዓ/ም ዐብይ ጾምና በዓላቱ

 ጥር 29 ቀን 2007 ዓ.ም.

የ2007 ዓ.ም. ዘመን አቆጣጠር በዓላትና አጽዋማትን በአዲሱ ዓመት መባቻ ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ አሁን ያለንበት ወቅት የነነዌ ጾም አልፈን ዐብይ ጾምን የምንቀበልበት ወቅት በመሆኑ መረጃውን ለማስታወስ ይህንን ዝግጅት ያቀረብን ሲሆን የምትፈልጉትን ቀን ለማወቅ ከማኅበሩ ድረ ገጽ ላይ ያለውን የዘመን መቁጠሪያ በመቀያየር መጠቀም ትችላላችሁ፡፡

 

የበዓላትና የአጽዋማት ኢየዐርግና ኢይወረድ

1. ጾመ ነነዌ ከጥር 17 ቀን በታች ከየካቲት 21 ቀን በላይ አይውልም
2. ዐቢይ ጾም ከየካቲት 1 ቀን በታች ከመጋቢት 5 ቀን በላይ አይውልም
3. ደብረ ዘይት ከየካቲት 28 ቀን በታች ከሚያዝያ 2 ቀን በላይ አይውልም፡፡
4. በዓለ ሆሣዕና ከመጋቢት 19 ቀን በታች ከሚያዝያ 23 ቀን በላይ አይውልም፡፡
5. በዓለ ስቅለት ከመጋቢት 24 ቀን በታች ከሚያዝያ 28 ቀን በላይ አይውልም፡፡
6. በዓለ ትንሣኤ ከመጋቢት 26 ቀን በታች ከሚያዝያ 3ዐ ቀን በላይ አይውልም፡፡
7. ርክበ ካህናት ከሚያዝያ 20 ቀን በታች ከግንቦት 24 ቀን በላይ አይውልም፡፡
8. በዓለ ዕርገት ከግንቦት 5 ቀን በታች ከሰኔ 19 ቀን በላይ አይውልም፡፡
9. ጾመ ሐዋርያት ከግንቦት 16 ቀን በታች ከሰኔ 20 ቀን በላይ አይውልም፡፡
10. ጾመ ድኅነት ከግንቦት 18 ቀን በታች ከሰኔ 22 ቀን በላይ አይውልም፡፡

 

ሁለት ዓይነት የተውሳክ አቆጣጠር አለ

 

1. የዕለት ተውሳክ በቅዳሜ ይጀምራል፡፡
የቅዳሜ ተውሳክ 8፤ የእሑድ ተውሳክ 7፤ የሰኞ ተውሳክ 6፤ የማክሰኞ ተውሳክ 5፤ የረቡዕ ተውሳክ 4፤ የሐሙስ ተውሳክ 3፤ የዓርብ ተውሳክ 2

 

2. የአጽዋማትና የበዓላት ተውሳክ
የነነዌ ተውሳክ 0፤ የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14፤ የደብረ ዘይት ተውሳክ 1፤ የሆሣዕና ተውሳክ 2፤ የስቅለት ተውሳክ 7፤ የትንሣኤ ተውሳክ 9፤ የርክበ ካህናት ተውሳክ 3፤ የዕርገት ተውሳክ 18፤ የጰራቅሊጦስ 28፤ የጾመ ሐዋርየት ተውሳክ 29፤ የጾመ ድኅነት ተውሳክ 1

 

በዓላትና አጽዋማት የሚውሉበት ቀን
– ጾመ ነነዌ
– ዐብይ ጾም
– ጾመ ሐዋርያት – ሰኞ

– ደብረ ዘይት
– ሆሣዕና
– ትንሣኤ
– ጰራቅሊጦስ – እሑድ

– ስቅለት -ዓርብ

– ርክበ ካህናት
– ጾመ ድኅነት -ረቡዕ

– ዕርገት -ሐሙስ ቀን ይሆናል፡፡

 

የ፳፻፯(2007)ዓ/ም 

ጾመ ነነዌ
  ጥር ፳፭ 
ዓብይ ጾም
   የካቲት ፱
ደብረ ዘይት
    መጋቢት ፮
ሆሳዕና
   መጋቢት ፳፯
ስቅለት
   ሚያዚያ ፪
ትንሣኤ
    ሚያዚያ ፬
ርክበ ካህናት
    ሚያዚያ ፳፰ 
ዕርገት
    ግንቦት ፲፫ 
ጰራቅሊጦስ
    ግንቦት ፳፫
ጾመ ሐዋርያት
   ግንቦት ፳፬ |