መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፡፡ (ዮሐ.16፡13)
ግንቦት 23ቀን 2007ዓ.ም
ዲ/ን ሚክያስ አስረስ
ይህች ዓለም ከእውነትን የራቀች መኖሪያዋን ሐሰት ያደረገች መሆኗ ይታወቃል፡፡ ሰው ማንነቱን አጥቶ በበደል ምክንያት በሐሰት ሰጥሞ ኖሯል፡፡ ሰው በፈቃዱ ጥመት ምክንያት ከሚፈጽማቸው በደሎች ትልቁ በደል ውሸት ነው፡፡ ውሸት ተሸንፎ ይወድቃል፤ ከሕይወት ይርቃል፡፡ የኀጣውእ ሁሉ ራስ ሐሰት ናት፡፡ ለዚህ ነው ክፋትን ከራሱ አንቅቶ የበደለ ዲያብሎስ አቡሃ ለሐሰት፤ የሐሰት አባት(ዮሐ.8፡44) የተባለው፡፡
የደሴ ማእከል የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ሊያካሂድ ነው
ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም
ከደሴ ማእከል
እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ ነው፡፡ ዕብ 11:1
ግንቦት 10ቀን 2007 ዓ.ም
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
እምነት የሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን ፔስቲስ የሚልውን የግሪክ ቃል የሚተካ ነው፡፡ ትርጉሙም አንድን ነገር መቀበልና ማሳመን ሞራላዊ ማረግጋገጫ መስጠት ማለት ነው፡፡ እምነት ማለት እውነትን መቀበልና ልባችንን ለዚህ እውነት መስጠት ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እምነት ተስፋ ስለምናደርገው እውነት የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው። “እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።” (ዕብ 11:1) እንዲል፡፡
ለአብነት መምህራንና ተማሪዎች ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ
ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም.
ከደሴ ማእከል
በማኅበረ ቅዱሳን ደሴ ማእከልና ደሴ ወረዳ ማእከል አስተባባሪነት ከሚያዚያ 18 â 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ከዘጠኝ ወረዳዎች ለተውጣጡ ዐሥራ ስምንት የአብነት መምህራንና ተማሪዎች ለሐዋርያዊ አገልግሎት የሚያበቃ ስልጠና ተሰጠ፡፡
ለካህናት የዐቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ
ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም.
ከደሴ ማእከል
በደሴ ከተማ ቤተ ክህነት፤ በማኅረ ቅዱሳን ደሴ ማእከልና ደሴ ወረዳ ማእከል አስተባባሪነት ሚያዚያ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ደሴ ከተማ ለሚገኙ ከሰባ በላይ ለሚደርሱ የደብር አስተዳዳሪዎች፣ ካህናት በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ የአንድ ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡
ለአብነት ተማሪዎች የአልባሳት ድጋፍ ተደረገ
ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም.
ከደሴ ማእከል
በማኅበረ ቅዱሳን ደሴ ማእከል የቅዱሳት መካናት ማኅበራዊ አገልግሎትና ልማት ክፍል አስተባባሪነት በሰሜን ወሎ ደላንታ እና መሀል ሳይንት ለሚገኙ የአብነት ተማሪዎች የአልባሳት ድጋፍ ተደረገ፡፡
በሊቢያ ለተሠዉ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የመታሰቢያ ጉባኤ ተካሄደ
ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም.
ዲ/ን ዘአማኑኤል አንተነህ(ከጎንደር ማእከል)
በሊቢያ ለተሠዉ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች በጎንደር ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የቆየ የመታሰቢያ ጉባኤ ተካሄደ፡፡
የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠናቀቀ
ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም.
ሚያዝያ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በጸሎት የተጀመረው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲካሔድ ቆይቶ ዛሬ ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ረፋድ ላይ ተጠናቅቆ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የጅማ ማእከል የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር እንደሚያካሄድ ገለጸ
ሚያዝያ 29 ቀን 2007 ዓ.ም.
በጅማ ማእከል
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ያስገነባው መንበረ ጵጵስና እና ጽ/ቤት ተመረቀ
ሚያዝያ 28 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገነባው ለመንበረ ጵጵስና እና ለጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል ባለ ሁለት ፎቅ ሕንፃ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሚያዝያ 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡