የበኬ ደብረ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የልማት ሥራ ተጎበኘ
ታኅሣሥ 1 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማዕከል ሥራ አሥፈጻሚ አባላትን ያቀፈ የልዑካን ቡድን በበኬ ደብረ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እየተከናወነ የሚገኘውን የልማት ሥራ ለመመልከትና ከደብሩ አስተዳደር አካላት ጋር ለመወያየት ኅዳር 23 ቀን 2005 ዓ.ም. ጉብኝት አካሄደ፡፡
የአዲስ አበባ ማእከል ከበኬ ደብረ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሰበካ ጉባኤ ጋር ባደረገው የውል ሥምምነት
መሠረት በባለሙያ አስጠንቶ ዘመናዊ የግብርና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብሮች ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በተያዘው እቅድ መሠረት እሰካሁን ከተከናወኑት ውስጥ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኑ ይዞታ በሆነው 3 ሄክታር መሬት ላይ የተዘራው የጤፍ እርሻ የሚገኝበትን መቃኘት የመጀመሪያው የጉብኝቱ አካል ነበር፡፡
የጤፉ እርሻ ለዓይን ይማርካል፡፡ ከ250 አስከ 300 ካሬ ሜትር የሚሆነው ከሌላው ማሳ ለየት ባለ ሁኔታ በቁመትም፤ ሆነ በያዘው የፍሬ መጠን ከፍተኛነት ይለያል፡፡ ለአጨዳ የደረሰ በሚመስል መልኩ ወደ ቢጫነት አዘንብሏል፡፡ ቀሪውም ባማረ ሁኔታ ጎልቶ ይታያል፡፡ ከፍተኛ ክትትል እንደተደረገበትም ያመለክታል፡፡
የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ገብረ አማኑኤል ቦታው ጠፍ የነበረና የከብቶች መዋያ ሆኖ መቆየቱንና ይህንንም ችግር ለመቅረፍ ከማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማዕከል ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት በባለሙያ ተጠንቶና ታርሶ ፍሬ ለማየት እንደበቁ የገለጹ ሲሆን ወደፊትም ተደጋግፎ የተሻለ ሥራ ለመሥራት እንደተዘጋጁ በጉብኝቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
“በእርሻ ሥራው ላይ የደብሩ ካህናት የንስሐ ልጆቻቸውን በማስተባበር፤ ለዘር የሚሆን ጤፍ በማቅረብ፤ በጉልጓሎና ዘር በሚዘራበት ውቅት ቤተሰቦቻቸውን ጭምር በማሰማራት፤ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ በመማር ላይ የሚገኙ ከ200 በላይ የአብነት ተማሪዎች፤ የደብሩ አስተዳደር፤ ካህናትና ዲያቆናት ተሳትፈውበታል፡፡ ምርቱም በመማር ላይ ለሚገኙት የአብነት ተማሪዎች የምግብ ፍጆታነት ይውላል” በማለት የገለጹት ደግሞ የቀድሞው የቤተ ክርስቲያኗ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ከፍያለው አየለ ናቸው፡፡
“የግብርና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብሮችን ለመጠቀም ጥረት አድርገናል፡፡ ለማስተማር የፈለግነው የአካባቢው አርሶ አደሮችና ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን በጎ ተሞክሮዎችን እንዲወስዱ ለማድረግ ነው፡፡ በበሬ ብቻ ሳይሆን በትራክተር እንዲታረስም አድርገናል፡፡ ከ3 ሄክታር መሬቱ ላይ ከ250 እሰከ 300 ካሬ ሜትሩ ለሙከራ ምርጥ ዘር ተጠቅመናል፡፡ የትኛው የተሻለ እንደሆነ ለሁሉም ለማሳየት የቻልንበት ነው፡፡ ገና ሳይታጨድ ልዩነቱም ጎልቶ ይታያል፡፡ በሚቀጥለው አመትም ጤፍ በመሥመር መዝራትን ተግባራዊ የምናደርግበት ሁኔታ እናመቻቻለን፡፡ ይህንን የምናደርገው ምእመናን የቤተ ክርስቲያናችንን ተሞክሮ ተመልክተው እነሱም እንዲጠቀሙበት ለማስተማር ነው፡፡” በማለት ወይዘሪት መቅደስ አለሙ በአዲስ አበባ ማእከል የማኅበራዊ አገልግሎትና ልማት ክፍል ሰብሳቢ በጉብኝቱ ላይ ገልጸዋል፡፡
በቀጣይነት የተካሄደው አብነት ትምህርት ቤቱ የሚገኝበት ሁኔታ ለመቃኘት የተደረገ ጉብኝት ነው፡፡ የአብነት ትምህርት ቤቱ በ3 መምህራን ከ200 በላይ ተማሪዎችን በማቀፍ የአቋቋም፤ የቅኔ፤ እንዲሁም የቅዳሴ ትምህርቶች የሚሰጥበት ተቋም ነው፡፡
በሁለት አዳራሾች ውስጥ መኝታቸውን ያደረጉት የአብነት ተማሪዎቹ የመኝታቸው ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ነው፤ አልጋቸው በርብራብ እንጨት
የተዘጋጁ ናቸው፤ የሳር ፍራሽና ካርቱን አንጥፈውበታል፡፡ አንዱን ከአንዱ ለመለየት በማዳበሪያ ተከፋፍሏል፤ በአንዱ አዳራሽ ውስጥ አዳራቸውን የሚያደርጉት ተማሪዎች ብዛት ከአንድ መቶ ይበልጣል፡፡ አዳራሹ ውስጥ እሳት ቢነሣ ወይም በሽታ ቢገባ የሚተርፍ ያለ አይመስልም፡፡ አንድ የማብሰያ ክፍል ሲኖር ሁሉንም ማስተናገድ ስለማይችል የተወሰኑት ተማሪዎች ውጪ ሜዳው ላይ ምግባቸውን ለማብሰል ይገደዳሉ፡፡
የቤተ ክተርስቲያኑ አስተዳደር ጉባኤ ያለውን ችግር በመረዳት ለሰንዳፋ በኬ የማኅበረ ቅዱሳን ማእከል፤ በቅደም ተከተልም ለአዲስ አበባና ለዋናው ማእከል የችግሩ አሳሳቢነት በማሳወቅ ጥናት ተደርጓል፡፡ በጥናቱ መሠረት የአብነት ትምህርት ቤቱን ለማደራጀትና ለማጠናከር ፤ ተማሪዎቹም ተምረው የነገዎቹ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሆኑ ለማስልቻል ጥረት በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ከፍተኛ በጀት በመመደብ የአብነት ትምህርት ቤቱን ዘመናዊ ሕንፃ ለመገንባት ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ግንባታውንም በዚህ ዓመት ይጀመራል ተብሎ እንደሚጠበቅ በጉብኝቱ ላይ ተገልጧል፡፡
በመጨረሻም በጋራ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሁሉም ድጋፍ እንደሚያስፈልግ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ገብረ አማኑኤል ጥሪያቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በልማት ሥራው ላይ ለተሣተፉ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ የሰንዳፋ ወረዳ ቤተ ክህነት ሓላፊዎች፤ የደብሩ አስተዳደር፤ ካህናትና ዲያቆናት፤ የደብሩ የሰበካ ጉባኤ አባላት፤ የማኅበረ ቅዱሳን የሰንዳፋ ማእከል ሓላፊዎችና አባላት፤ ጥሪ የተደረገላቸው የአጥቢያው ምእመናን ተገኝተዋል፡፡
በኬ ደብረ ምሕረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት በ1860ዎቹ ውስጥ እንደ ተተከለ ይነገራል፡፡




የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ሙሉጌታ ኃይለ ማርያም የወርቅ ሜዳልያውን በተረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት “የማኅበረ ቅዱሳን አባላት በግቢ ጉባኤያት ቆይታቸው በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የተሸለሙትን ሜዳልያ ለማኅበሩ ሲያበረክቱ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ኅዳር 22 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ስዓት ላይ በማኅበሩ ሕንፃ ላይ ተካሄደ፡፡
የውይይት መድረኩ በአቶ ወንድወሰን አዳነ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ሥነ ጽሑፍ ትምህርት ክፍል መምህር የተመራ ሲሆን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ለውይይት መድረኩ መነሻ የሚሆን ጥናታዊ ጽሑፋቸውን አቅርበዋል፡፡ ባቀረቡት ጽሑፍም “ሥነ ፍጥረት የሚነበብ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፍ እግዚአብሔር በመጀመሪያ ለፍጥረቱ የሰጠው ትልቁ ሥጦታ ነው፡፡” በማለት የጥናት ጽሑፋቸውን በመጀመር በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ መጻሕፍት የተነገሩትን ጠቅሰዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል” በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ፀኑ፤ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ የባሕርን ውኃ እንደ ረዋት የሚሰበስብ ቀላዮችንም በመዝገቦች የሚያኖራቸው” መዝ.86፤6 “በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ አንብቡም አፌ አዟልና” (ኢሳይያስ 34፤16) በማለት ጠቅሰዋል፡፡ በተጨማሪም ከቅዱሳን አበው መካከል “ቅዱሳት መጻሕፍትን አለማወቅ የስህተት ሁሉ ምንጭ ነው” በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከተናገረው በመነሣት የቅዱሳት መጻሕፍት ጠቀሜታን አብራርተዋል፡፡
ጥናቱ ከቀረበ በኋላም በንባብ ባሕል ላይ ያተኮረ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የዩኒቨርስቲ ምሁራንና ተማሪዎች እንዲሁም ተሳታፊዎች አስተያየቶቻቸውንና የመፍትሔ አሳቦቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በአብዛኛው ከተጠቀሱት ውስጥም የንባብ ባሕላችንን ለማሳደግ በዋነኛነት ቤተሰብና ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ሓላፊነት እንዳለባቸው ፤ ልጆች ከሕፃንነት ጀምሮ ንባብን ባሕል አድርገው እንዲያድጉ ከፍተኛ ሥራ መሠራት እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡
የአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድሥት ሥላሴና አቡነ ሳሙኤል ገዳም 6 ኪሎ ሜትር የተራራው መውጫ መንገድ በሁለት በጎ አድራጊ ወጣቶች ሙሉ ወጪውን በመሸፈን የጥርጊያ መንገዱን ሥራ ከመስከረም 7 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በ17 ቀናት ውስጥ በመሥራት ተጠናቀቀ፡፡
ሥራውን ለመሥራት በገዳሙ በቆዩባቸው ጊዜያት ያስተዋሉትን ሲገልጹም “የገዳማውያኑ ስሜት ልዩ ነው፡፡ የገዳማውያን አባቶችና እናቶች ደስታ ተመልክተናል፡፤ እንኳን እነሱ ለዘመናት የተቸገሩት ቀርቶ እኛም የተሰማን ስሜት መግለጽ ከምንችለው በላይ ነው፡፡ ደስታቸው አስደስቶናል፡፡ ሰዎች ለእግዚአብሔር በሰጡ ቁጥር የሚጎድልባቸው የሚመስላቸው አሉ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የተሻለ ነገር እንደሚሰጣቸው ማመን አለባቸው፡፡ ለእግዚአብሔር መስጠት አያጎድልም ይጨምራል እንጂ፡፡ የእኛን ደስታ ሌሎችም እንዲጋሩት እንፈልጋለን፡፡ ያደረግነው ነገር ትንሽ ቢሆንም ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንክ ትረካለህ፡፡ ወደፊትም አቅማችን እያዳበርን ሌሎች ገዳማትን የመርዳት እቅድ አለን፡፡” በማለት ሁለቱ በጎ አድራጊ ወጣቶች ተናግረዋል፡፡
በቤተ እስራኤል ስም ጠባይን፣ ግብርን፣ ሁኔታን እንደሚገልጥ ሁኖ ይሰየማል፡፡ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም “ማርያም” የሚለውን ስያሜ ከማየታችን በፊት ስለ ድንግል ማርያም አባቶቻችን በነገረ ማርያም ያሉትን ጥቂት እንመለከታለን፡፡ “ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ በም.1፥9 ላይ እንደተናገረ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ነበር፡፡” እንዳለ በኦ.ዘፍ.ም.19፥1 ጀምሮ እንደተጻፈ የሰዶምና የገሞራ ሰዎች በበደላቸው ምክንያት እንደተደመሰሱ /እንደጠፉ/ እናነባለን፡፡ አዳምና ልጆቹ በሲዖል ባህር ሰጥመን እንዳንቀር እግዚአብሔር በቸርነቱ ንጽህት የሆነች ዘር መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እያማለደች የምታሰጥ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ባያስቀርልን ከእርሷም መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን የሚያርቅ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ የሚያድል የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ተወልዶ በሞቱ ሞታችንን ባይደመስስ ወደ ሕይወት ባይመልሰን ኖሮ መኖሪያችን ሲዖል ነበር፡፡
በሲዳሞ ክፍለ ሀገር፣ ቡሌ ወረዳ በሚገኘው ጎንፈራ ቀበሌ፥ ከወላጅ አባታቸው አቶ ውቤ አብዲና ከእናታቸው ከወ/ሮ መሰለች ተመስገን፥ መጋቢት 5 ቀን 1955 ዓ.ም የተወለዱት ዲ/ን ረዳ ውቤ፤ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በልዩ ልዩ የሕክምና መስጫ ተቋማት ሲረዱ ቆይተው በ50 ዓመታቸው ኅዳር 10 ቀን 2005 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተው፥ ኅዳር 11 ቀን 2005 ዓ.ም በቡራዩ ፄዴንያ ስመኝ ማርያም ገዳም ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል፡፡
