የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ ለማሳካት የገዳማት ድርሻ!!

  • የወርቃማው ዘመን ወርቃማ ደራሲ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የገድል መጽሐፍ  ይመረቃል

 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን ጥንታውያን ገዳማት እና የአብነት ትምህርት ቤቶች ለማጠናከር ላለፉት 10 ዓመታት ዘላቂ የልማት ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ከምዕመናን በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚህም አበረታች ውጤት ተመዝግቧል፡፡

 

ማኅበሩ ይህንን አገልግሎት አጠናክሮ ለመቀጠል ከ50 ጥንታውያን ገዳማት የተውጣጡ አበምኔቶች በተገኙበት “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ ለማሳካት ገዳማት ያላቸው ድርሻ ”  በሚል መሪ ቃል ቅዳሜ ታኅሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ስብሰባ ማዕከል በተቀናጀ ልማት ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል፡፡

 

እርስዎም በዕለቱ ተገኝተው የመርሐ ግብሩ ተሳታፊ በመሆን የአባቶችን ቡራኬ በመቀበል ድርሻዎትን ይወጡ ዘንድ በአክብሮት ተጋብዘዋል፡፡

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

አድራሻ ፡- ስድስት ኪሎ ከምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ከፍ ብሎ በኢትዮጵያ ስብሰባ ማዕከል
አዘጋጅ ፡-የማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል