ሰሙነ ሕማማት(ለህጻናት)
ሚያዚያ 1/2004 ዓ.ም.
እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? ደህና ናችሁ? እንኳን ለሰሙነ ሕማማት በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ልጆች ሰሙነ ሕማማት ምን ማለት እንደሆነ ታውቃላች? ሰሙነ ሕማማት ከትንሣኤ በፊት ያለውን ሳምንት ሲሆን በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን የሰው ልጆች ለማዳን ሲል የተቀበለውን መከራ ከሌላ ጊዜ በተለየ መልኩ የምናስብበት ሳምንት ነው፡፡ ጌታችን በዚህ ሳምንት ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ የተለያዩ ተግባራት አከናውኗል፡፡ እስኪ ልጆች ቀናቱንና በቀናቱ ውስጥ የተፈጸሙትን ተግባራት በዝርዝር እንመልከት፡-
1. እሑድ /ሆሣዕና/፡- በዚህ ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርቦ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ይከተሉት የነበሩት ሰዎች በተለይም ሕፃናት ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ብለው እየዘመሩ ጌታችንን አመስግነውታል፡፡
- ጌታችን እርቦት ስለነበር ወደ አንዲት በለስ ሄደ፡፡ በለሷ ግን ቅጠል ብቻ ሆና ፍሬ አላገኘባትም ነበር፡፡ ያቺ በለስም ዳግመኛ ፍሬ እንዳታፈራ ረገማት፡፡
- ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን ሰዎች አስወጣቸው፡፡
– ልጆች በዚህ ዕለት ማር.11÷12-19 እና ሉቃ.19÷45-46 ላይ የሚገኘውን የወንጌል ክፍል አንብቡ፡፡
- የካህናት አለቆች ጌታን ሊሰቅሉት ተማክረዋል
- ጌታ በስምዖን ቤት ተገኝቶ ሳለ አንዲት ሴት ሽቶ ቀብታዋለች፡፡
- ይሁዳ የተባለው ሐዋርያ ጌታን ለካህናት አለቃ አሳልፎ ለመስጠት በ30 ብር ተስማምቷል፡፡
- ጌታ የሐዋርያትን እግር አጠበ
- የቊርባንን ሥርዓት ሠራ
- በዮሐንስ ወንጌል ምራፍ 17 ላይ ያለውን ረጅም ጸሎት በጌቴ ሴማኒ ጸለየ፡፡
- በዚህ ዕለት ሌሊት ይሁዳ ጌታን አሳልፎ ለካህናት አለቆች ሰጠው፤ ወታደሮችም ያዙት፡፡
– በዚህ ዕለት ዮሐ.18÷1-12፣ ሉቃ.22÷7-53፣ ማቴ.26÷17 ላይ የሚገኘውን የወንጌል ክፍል አንብቡ፡፡
- የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ በማለቱ በጲላጦስ ፊት በሐሰት ከሰሱት፡፡ በዚህ ዕለት ጌታችን ስለ እኛ ሲል ተሰቀለ፡፡ በሰዎች ፈንታ ሞትን ተቀበለ፡፡