‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› (ዮሐ. ፲፥ ፲፮)
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንቀጸ አባግዕ ሲያስተምር ‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› ብሏል።(ዮሐ. ፲፥ ፲፮)
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንቀጸ አባግዕ ሲያስተምር ‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› ብሏል።(ዮሐ. ፲፥ ፲፮)
በቅዱስ ዮሐንስ እጅ በማየ ዮርዳኖስ ተጠምቆ የባሕርይ ልጅነቱንና አምላክነቱን ከአብ እና ከመንፈሰ ቅዱስ አስመሰከረ፡፡
አስተርእዮ መታየት ወይም መገለጥ የሚል ትርጓሜ ያለው የግእዝ ቃል ነው፡፡ በግሪክ ‹‹ኤጲፋኒ›› የሚል ስያሜ አለው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትም ይህን ቃል በመጠቀም ኤጲፋኒያ እያሉ በዜማ መጻሕፍቶቻቸው ይጠሩታል፡፡
በዚህ ጊዜ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹‹አባት ሆይ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው፤ ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ›› አለ፡፡ ያንጊዜም ያለ ሰው እጅ በጌታችን ላይ ግዝረት ተገለጠ (የግዝረት ምልክት ታየ)፡፡
በአሁኑ ወቅት በአንድም በሌላ አንዳንድ የይዘት፣ የትርጉም፣ የፍቺ ግድፈቶች ከዛ የባሰም የዶግማ ችግር ያለባቸው ለቤተክርስቲያን ትምህርት ስጋት የሆኑ ከስንዴ መሐል የተቀላቀሉ ጥቂት እንክርዳድ የተቀላቀለባቸው መጻሕፍት በቤተ ክርስቲያን ስም እየወጡ ነው፡፡ ስለዚህ እንክርዳዱን ከስንዴው ለቅሞ መለየትና ማረም ያስፈልጋል፡፡
ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው ‹‹የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ÷ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ፡፡ እኔም እልሃለሁ÷ አንተ ጴጥሮስ ነህ፤ በዚያች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ÷ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም፡፡››(ማቴ.፲፮፥፲፫—፳)
ለአምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን በዓለም ላይ ሠልጥኖ የነበረውን ጨለማ ያስወግድ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ሰው ሆነ፡፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው አማናዊው ብርሃን ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ በሥጋ ተገለጠ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴው እንዳለው ‹‹ብርሃን ዘበአማን ዘያበርህ ለኵሉ ሰብእ ለእለ ይነብሩ ውስተ ዓለም፤ በጨለማ ውስጥ ለሚኖር ሕዝብ ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው›› (ኢሳ. ፱፥፪)፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሚታወሱባቸው በዓላት መካከል ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የሚከብረው በዓለ ልደታቸው አንደኛው ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ዜና ልደታቸውን ሲናገር ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› በማለት በክብር ጠርቷቸዋል፡፡
ብሥራታዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በአምሳለ አረጋዊ እንዲህ አላት ‹‹ደስ ይበልሽ÷ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ÷ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው፤ ከሴቶች መካከል አንቺ የተባረክሽ ነሽ፡፡›› (ሉቃ. ፩፥፳፰-፳፱) ድንግል ማርያምም ‹‹እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንዴት ይደረግልኛል?›› ብላ ጠየቀችው፡፡
በየዘመኑ የተነሡ ነቢያትም ምንም እንኳን አምላክ ይህን ዓለም እንዴት እንደሚያድነው በግልጽ ባይረዱትም እግዚአብሔር ዓለሙን የሚያድንበትን ቀን እንዲያቀርበው እንዲህ እያሉ ይማፀኑ ነበር፤ ‹‹አቤቱ ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አድርጋቸው፤ ውረድም፤ ተራሮችን ዳስሳቸው ይጢሱም፡፡ መብረቆችህን ብልጭ አድርጋቸው፤ በትናቸውም፤ ፍላጾችን ላካቸው፤ አስደንግጣቸውም፡፡ እጅህን ከአርያም ላክ፤ አድነኝም›› (መዝ. ፻፵፫፥፭-፯)፡፡