ደብረ ምጥማቅ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የበዓለ ሃምሣ ሳምንታት እንዴት ናቸው? ቤተ ክርስቲያን እየሄዳችሁ ታስቀድሳላችሁ? በሰንበታትስ ከወላጆቻችሁ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ትሄዳላችሁ? ከሆነ በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደብረ ምጥማቅ በሚባል ገዳም ያደረገችውን ተአምር ነው፤

“በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ” (የዘወትር ጸሎት)

በጉባኤ ኒቅያ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት“ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ወነበረ በየማነ አቡሁ…፤ በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ…” እንዳሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በኋላ በአርባኛው ቀን በዚህ ዓለም የነበረውን የማዳኑን ሥራ ጨርሶ ወደ ላይ ማረጉንና በቀደመ ክብሩ በአብ ቀኝ መቀመጡን በማሰብ በዘወትር ጸሎታችንም እንዘክረዋለን፡፡

‹‹ተዝካረ ዕረፍቱ ለቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ››

ዐሥራ ሁለተኛው የቊስጥንጥንያ መንበር የነበረ፣ ከአራቱ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያን ዐቃቢያነ እምነት ከሆኑት ከቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ከቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያና ከቅዱስ ባስልዮስ ጋር በግብር የተካከለ፣ በገዳማዊ ሕይወቱ ብሕትው፣ በንጽሕናው ተአማኒ፣ በአእምሮ ምጡቅ፣ በአንደበቱ ርቱዕ፣ በስብከቱ መገሥጽ፣ በፍርዱ ፈታሒ በጽድቅ፣ በመግቦቱ አበ ምንዱባን (የድኆች አባት) በጥብቅናው ድምፀ ግፉዓን፣ በጥቡዕነቱ መገሥጽ፣ በክህነቱ የቤተ ክርስቲያን መዓዛ፣ የዓለም ሁሉ መምህር የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዕረፍቱ መታሰቢያ በግንቦት ፲፪ ቀን ሆነ።

ማይኪራህ

ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤

ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ

ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ፣ የዜማ ደራሲና ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ድንቅ ተጋድሎን ፈጽሞ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም የገባበት ዕለት ግንቦት ፲፩ የከበረች እንደመሆኗ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡

ልደታ ለማርያም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን? በርቱ! ዛሬ የምንነጋራችሁ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ይሆናል!መልካም ንባብ!

ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ

ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ የሆነበት ቀን ሚያዚያ ፳፫ የከበረ ነው፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስ አባት ቀጰዶቅያ አገር ይኖር የነበረ አንስጣስዮስ የተባለ መስፍን ነው፡፡ እናቱም ቴዎብስታ የተባለች ፍልስጥዔማዊ ነበረች፤ የዚህ ቅዱስ አባትም የሞተው በልጅነቱ ስለዚህም ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ አሳደገው፡፡ መስፍኑም በጦር ኃይል አሰለጠነው፡፡ ሃያ ዓመትም በሞላው ጊዜ መስፍኑ የ፲፭ ዓመት ልጁን ሊያጋባውና ሀብቱን ሊያወርሰው ድግስ ደገስ፤ ነገር ግን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዚህ አልመረጠውምና  የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ከጨርሰ በኋላ ወደ ቤሩት ሀገር ሄደ፡፡ በዚያም ደራጎንን ያመልኩና ሴት ልጆቻቸውን ይገብሩለት ነበር፤ ሰማዕቱም ደራጎኑን በኃይለ መስቀል ድል ነሥቶት ገድሎታል፤ ሕዝቡንም ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሷቸዋል፡፡

የኤማኁስ መንገደኞች

በዓለም ላይ ብዙ መንገዶች አሉ፤ ሰዎችም በመንገድ ይጓዛሉ፤ ሆኖም ለተለያየ ዓላማ ነው፤ ግን ያች የኤማኁስ መንገድ ምን ያህል ዕድለኛ ናት? ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት የሚወራባት፣ ክርስቶስ በእግሩ እየባረከ የነቢያትን ትምህርት የሚተረጉምባት መንገድ፣ የጠወለገ የደከመ የሚበረታባት መንገድ!

ነገረ ትንሣኤ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? እንኳን አደረሳችሁ! የትንሣኤ በዓል እንዴት እያከበራችሁ ነው? መልካም! ልጆች! ዛሬ ስለ ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ እንማራለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን ከትንሣኤ በዓል ጀምሮ እስከ በዓለ ሃምሣ ድረስ ስንገናኝ የምንለዋወጠውን ሰላምታ እናስቀድም!

ዘመነ ትንሣኤ

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ከሚከበርበት ዕለተ እሑድ አንሥቶ እስከ የሚቀጥለው እሑድ ያሉት ቀናት ለእያንዳንዳቸው ዕለታት ስያሜ ተሰጥቷቸው ፍቅሩን እያሰብን ውለታውን እያስታወስን እናዘክራቸዋለን፡፡