ፅንሰታ ለማርያም
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናት ቅድስት ሐና የተወለደችው በቤተ ልሔም ይሁዳ ውስጥ ነው፡፡ ኢያቄም የሚባል ሰው አግብታ ትኖር ነበር፡፡ ሁለቱም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን ሐና መካን ስለነበረች ልጅ መውለድ አልቻሉም፡፡ በዚህም ለበርካታ ዓመት ሲያዝኑና አምላካቸውን ሲማጸኑ ኖሩ፡፡ በዚህም መካከል ስዕለትን ተሳሉ፤ ፈጣሪ ልጅ ቢሰጣቸው ለቤተ ክርስቲያን አገልጋይ እንደሚሰጡም ቃል ገቡ፡፡