‹‹በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይሰበስባሉ›› (መዝ.፻፳፭፥፭)

የሰው ልጅ በዚህ ምድር ከሚፈራረቁበት የስሜት ነጸብራቆች ዋነኞቹ ኀዘን (ልቅሶ)ና ደስታ ናቸው። እርግጥ ነው እግዚአብሔር የሰውን ልጅ የፈጠረው እያመሰገነው በደስታ ይኖር ዘንድ ነበር፡። ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን የሚያስፈልገውን ሁሉ ካዘጋጀለት በኋላ በአትክልት ሥፍራ ኤደን ገነት በደስታ እንዲኖር አስቀመጠው፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ በገዛ ፈቃዱ ደስታ የሚሰጠውን ሕግ አፍርሶ የደስታ ምንጭ የሆነውን እግዚአብሔርን አጣ፤ በማጣት ብቻም አልቀረም ‹‹…ስለዚህ የተገኘባትን መሬት ያርስ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ደስታ ከሚገኝባት ገነት አስወጣው…›› (ዘፍ. ፫÷፳፫)። የሰው ልጅ በድሎ ከኤደን ገነት ወደ ምድር (ዓለመ መሬት) ከመጣ በኋላ እግዚአብሔርን አሳዝኖ ጸጋውን አጥቷልና በሕይወቱ ኀዘን (ልቅሶ) ሰፊውን ጊዜ የሚወስድበት ፍጡር ሆነ። ለ፭ሺ ፭መቶ ዘመን የሰው ልጅ ፍጹም በሆነ ኀዘን ውስጥ ከኖረ በኋላ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ተዋሕዶ በመገለጥ ለአዳም (ለሰው ልጅ) ካሣ በመሆን ወደ ፍጹም ደስታ መልሶታል።

ተስፋ

ሕይወታችን ያለ ተስፋ ባዶ ነው፤ ያለ ተስፋ መኖር አንችልም፤ ተስፋ ከሌለን ማንኛውንም ዓይነት የኑሮ ገጠመኝና ችግር ማሳለፍ አይቻለንም፡፡ የሰው ልጆች ዋነኛው ብርታት ተስፋ ማግኘትና በተስፋ መኖር ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው አዳም የአምላካችን የእግዚአብሔርን ሕግ ተላልፎ አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ ከበላ በኋላ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በምድር ላይ ሲኖር በኀዘንና በጭንቅ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፈጣሪ የልቡን ጭንቀትና ኀዘን ተመልክቶ ሊምረው ስለወደደ ከልጅ ልጁ ተወልደ እንደሚያድነው ቃል ገባለት፡፡ ይህም ለአዳም ትልቅ ተስፋ ስለነበረ ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ በተስፋ ጠብቋል፡፡

‹‹አናቅጸ ሲኦል ኢይኄይልዋ፤ የገሃነም ደጆች አይችሏትም›› (ማቴ.፲፮፥፲፱)

በፊልጶስ ቂሳርያ ‹‹ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል›› ብሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጠየቀ ሰዓት የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ የተናገረው ቃል ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ሆነ ነው፡፡ (ማቴ.፲፮፥፲፫) ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነህ›› በማለት በሰጠው ምስክርነት ጌታችን ‹‹የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ …..አንተ ዓለት ነህ፥ በዚያችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም›› በማለት ለሐዋርያቱ ቃል ኪዳን ገባላቸው። (ማቴ.፲፮፥፲፰) ቤተ ክርስቲያን የሚለው የተለያየ ዐውዳዊ ፍች ቢኖረውም የሰውን ድካም የሚያውቅ እግዚአብሔር በዚህች ቀን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በፊልጵስዩስ ከሦስት ደንጊያዎች ቤተ ክርስቲያንን ሠራልን። ዓለት ያለውን ቅዱስ ጴጥሮስንም ‹‹አርሳይሮስ›› ብሎ ሾመው፤ ትርጓሜውም ሊቀ ጳጳሳት ማለት ነው። (መጽሐፈ ስንክሳር፣ ሰኔ ወር፣ ፳ እና ፳፩ ቀን)

ቅዱስ ወንጌል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን አላችሁ? ጾመ ሐዋርያትን እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? ልጆች! ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፤ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፡፡…ልጆች! ዛሬ ስለ ቅዱስ ወንጌል እንማራለን፤ መልካም ንባብ!!!

‹‹ወደ ዕረፍት አወጣኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)

አባቶቻችን እስራኤላውያን በግብፅ ሳሉ የደረሰባቸውን መከራና ሥቃይ በመንፈስ ቅዱስ ረዳትነት የተመለከተውን እና ያየውን ታሪክ ነቢዩ ዳዊት ግልጽ አድርጎ ጽፎልናል። ከእሳትና ከውኃ መካከል እንዳወጣቸው እንዲሁም ዕረፍትን እንዴት እንዳገኙ በዚሁ ክፍል ተመዝግቦ እናገኘዋለን።

‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ ያድናቸውማል›› (መዝ.፴፫፥፯)

ልበ አምልክ ቅዱስ ዳዊት የተናገረው ይህ ኃይለ ቃል እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ጠባቂ መልአካቸው በዙሪያቸው ሰፍሮ የሚጠብቃቸው መሆኑን የሚገልጽ ነው፡፡ ሰዎች የሚጠበቁት በሦስት በኩል ነው፤ …. በየዓመቱ በዓለ ቅዱስ ሚካኤል የሚታሰበው በዓል የመላእከትን ጥበቃ መሠረት ያደረገ ነው፡፡

‹‹ትዕግሥትን ልበሱ›› (ቈላ.፫፥፲፪)

በሕይወታችን ውስጥ እጅጉን አስፈላጊ መጨረሻውም አስደሳች የሆነው ነገር ትዕግሥት ነው፤ በማንኛውም ሁኔታና ጊዜ ሆነን የምንጋፈጠውን ችግር፣ መከራና ሥቃይ በብርታትና በጽናት ለማለፍ የምንችለው ትዕግሥተኛ ስንሆን ነው፡፡ መታገሥ ከተቃጣ ሤራ፣ ከታሰበ ክፋት፣ ከበደልና ግፍ ያሳልፋል፤ ልንወጣው ከማንችለው ችግርም እንድንወጣ ይረዳናል፡፡

ትጋት

የክርስቲያናዊ ምግባራችን ጽናት ከሚገለጽባቸው ዋነኞቹ ተግባራት መካከል ትጋት አንዱ ነው፡፡ ጸሎትን፣ ጾምንና ስግደትን በማብዛት የሚገለጸው ትጋታችን ክርስትናችንን የምናጠነክርበት ምግባራችን ነው፡፡ ዘወትር ሥርዓተ ጸሎትና ጾምን ጠብቀን መኖራችን በመንፈሳዊ ሕይወታችን ጠንክረንና ማንኛውንም ፈተና አልፈን እንድናንጓዝ ይረዳናልና ትጋታችንን ማጠንከር የምንችለው ዕለት ከዕለት ስንጸልይ፣ በሥርዓት ስንጾምና አብዝተን ስንሰግድ ነው፡

‹‹ሐሰትን አትነጋገሩ›› (ሌዋ.፲፱፥፲፩)

ከሁሉም አስቀድሞ ሰዎች ፈጣሪ እግዚአብሔር የእውነት አምላክ እንደሆነ ልንረዳ ይገባናል፡፡ እርሱ እውነተኛና የእውነት መንገድ እንደሆነ ስንናውቅ መንገዳችን በእውነትና ስለ እውነት ይሆናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ›› በማለት እንደተናገረው በሕይወታችን ውስጥ እውነትን ማሰብ፣ እውነትን መናገር እንዲሁም በእውነተኛው መንገድ መጓዝ የሚቻለን አምላካችን እውነተኛ መሆኑንና ሐሰትን እንደሚጠላ ስናውቅ ነው፡፡ (ዮሐ.፲፬፥፮)

ቅዱስ አማኑኤል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁልን?  ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን! አሜን! (መዝ.፳፪፥፲) ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ስለጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘አማኑኤል’ ስለሚለው ስሙ ትርጉም ይሆናል!