“በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ” (የዘወትር ጸሎት)

በጉባኤ ኒቅያ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት“ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ወነበረ በየማነ አቡሁ…፤ በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ…” እንዳሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በኋላ በአርባኛው ቀን በዚህ ዓለም የነበረውን የማዳኑን ሥራ ጨርሶ ወደ ላይ ማረጉንና በቀደመ ክብሩ በአብ ቀኝ መቀመጡን በማሰብ በዘወትር ጸሎታችንም እንዘክረዋለን፡፡

‹‹ተዝካረ ዕረፍቱ ለቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ››

ዐሥራ ሁለተኛው የቊስጥንጥንያ መንበር የነበረ፣ ከአራቱ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያን ዐቃቢያነ እምነት ከሆኑት ከቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ከቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያና ከቅዱስ ባስልዮስ ጋር በግብር የተካከለ፣ በገዳማዊ ሕይወቱ ብሕትው፣ በንጽሕናው ተአማኒ፣ በአእምሮ ምጡቅ፣ በአንደበቱ ርቱዕ፣ በስብከቱ መገሥጽ፣ በፍርዱ ፈታሒ በጽድቅ፣ በመግቦቱ አበ ምንዱባን (የድኆች አባት) በጥብቅናው ድምፀ ግፉዓን፣ በጥቡዕነቱ መገሥጽ፣ በክህነቱ የቤተ ክርስቲያን መዓዛ፣ የዓለም ሁሉ መምህር የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዕረፍቱ መታሰቢያ በግንቦት ፲፪ ቀን ሆነ።

ማይኪራህ

ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤

ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ

ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ፣ የዜማ ደራሲና ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ድንቅ ተጋድሎን ፈጽሞ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም የገባበት ዕለት ግንቦት ፲፩ የከበረች እንደመሆኗ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡

‹‹ኑ ምሳ ብሉ›› (ዮሐ.፳፩፥፲፪)

ይህን ኃይለ ቃል የተናገረው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ቃሉን  ደግሞ የሚበላ ፈልገው ዓሣ ለማጥመድ ሌሊቱን ሲደክሙ ለነበሩ ግን የሚፈልጉትን ሳያገኙ በረኀብ ዝለው በፍለጋ ደክመው ለነበሩ ለቅዱሳን ሐዋርያት ነው፡፡ ሞትን በሞቱ ገድሎ፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችንን አብሥሮ፣ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻ ተገለጠላቸው፤ ይህ ከትንሣኤው በኋላ ሲገለጥላቸው ሦስተኛው ጊዜ ነው፡፡ መጀመሪያ ሲገለጥላቸው አይሁድን ፈርተው በፍርሃት ተሸብበው በራቸውን ዘግተው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ በነበሩ ጊዜ በዝግ ቤት ገብቶ ፍርሃትን አስወገደላቸው ተስፋቸውን ቀጠለላቸው፤ ለተረበሸው ልባቸው ‹‹ሰላም ለእናንተ ይሁን›› በማለት ሰላምን ሰጣቸው አረጋጋቸው፡፡ (ሉቃ.፳፬፥፴፮፣ዮሐ.፳፥፲፱)

“ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.፲፫፥፴፬)

መውደድ በሰዎች መካከል የሚኖር ስሜት ነው፤ ያለ መዋደድም በዚህ ምድር ላይ መኖር አይቻለንም፤ መጠኑ ይብዛም ይነስ በሰው ልብ ውስጥ የመዋደድ ስሜት ይፈጠራል፡፡ ሰዎች ተቻችለንና ተሳስብን እንዲሁም ተዛዝነን የምንኖረው ስንዋደድ ነው፡፡ ግን ይህ ስሜት ከምንም ተነሥቶ በውስጣችን ሊፈጠር አይችልምና መውደድ መነሻው ምንድነው? የሚለውን ነገር ብንመረምር መልካም ነው፡፡

የትዕግሥት ፋና

ኢዮብ ጻድቅ ሰው ነው

ምክር የመከረ

ኢዮብ ፍጹም ሰው ነው

የትዕግሥት ፋና

በገድል የከበረ!

“የሕይወት ቀን” በግቢ ጉባኤያት

ወርቃማው የወጣትነት ዘመናችን በተስፋ፣ በመልካም ምኞትና በትጋት የተሞላ፣ ዕውቀትንና አቅምን ያማከለ ማንነታችን የሚታነጽበት፣ መንፈሳዊነታችን የሚገለጽበት የዕድሜ ክልል እንደመሆኑ የሕይወታችን መሠረት ነው፡፡ መንፈሳዊ ፍሬን አፍርተን ርስተ መንግሥተ ሰማያት ለምንወርስብትም የሕይወት ስንቅ የምንሰንቅበት የተጋድሎ ዘመን ስለመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከልጅነታችን ጀምሮ አበክራ ታስተምረናለች፡፡ በሰንበት ትምህርት ቤቶቿም ኮትኩታ አሳድጋ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት ታበቃናለች፡፡ ለዚህ የመሸጋገሪያ ዕድሜ በደረስንበት ጊዜም የሕይወታችን መርሕ የሆነው ትምህርተ ወንጌል እንዳይጓደልብን በዐውደ ምሕረቷ ላይ ጉባኤ ዘርግታ ሰማያዊ ኅብስትን አዘጋጅታ ትመግበናለች፡፡

ልደታ ለማርያም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን? በርቱ! ዛሬ የምንነጋራችሁ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ይሆናል!መልካም ንባብ!

“በክፉዎች መንገድ አትሂድ” (ምሳ.፬÷፲፬)

እግዚአብሔር መላእክትንና የሰው ልጅን ሲፈጥር የፈጠረበት ትልቁ ዓላማ ስሙን ቀድሰው ክብሩን እንዲወርሱ ነው፤ ነገር ግን ክፋትን ኃጢአትን ዲያብሎስ (አስቀድሞ ሳጥናኤል የተባለ) ከልቡ በሐሳቡ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለመ መላእክት አመነጫት፤ አመንጭቶም አልቀረም፤ ከራሱ ጋር ሌሎች እርሱን የመሰሉ መናፍስትን (መላእክትን) ይዞ ከሰማያዊ ክብሩ ወደቀ::