‹‹ስለምጽፍላችሁ ነገር እነሆ በእግዚአብሔር ፊት ሐሰት አልናገርም›› (ገላ.፩፥፳)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? መምህራን የሚነግሯችሁን በትኩረት በማዳመጥ፣ መጻሕፍትን በማንበብና ያልገባችሁን በመጠየቅ ትላንት ከነበራችሁ ግንዛቤ የተሻለ ዕውቀትን እየቀሰማችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! መልካም!
ውድ የእግአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት በዓላትን አስመልክተን የቅዱሳንን ታሪክ አዘጋጅተን ባቀረብንላችሁ መሠረት ከቅዱሳን የሕይወት ታሪክ በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? በተለይ ሥርዓትን አክብረን መኖረ እንደሚገባን፣ በቤተ እግዚአብሔር መኖር ደግሞ ታላቅ በረከትን እንደሚያስገኝልን፣ ለቅዱሳን ስለተሰጣቸው ክብርና የቅድስና ሕይወታቸው ምን እንደሚመስል ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ያዘጋጀንላችሁ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ትምህርት ሲሆን ሐሰት መናገር እንደማይገባ እንዲሁም እውነተኛና ታማኝ መሆን እንዳለብን ልናስተምራችሁ ወደድን፤ በጥሞና ተከታተሉን!