ቅዱስ ዑራኤል በግሸን አምባ
ጥቅምት 29 ቀን 2005 ዓ.ም.
በመምህር ሳሙኤል ተስፋዬ
- ‹‹መስቀሉ በአዳል ሜዳ በር እንዲገባ ያመላከተው ቅ/ ዑራኤል ነው››
- ‹‹ጥር 22 ቀን ቤተ ክርስቲያኑ ይመረቃል››
ቅዱስ ተብለው የሚጠሩት ደገኛው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ካሌብ የሀገረ ናግራን ክርስቲያኖችን ለመታደግ ዘምተው የአሕዛቡን ንጉሥ ፊንሀስን ድል አድርገው ሲመለሱ በነበራቸው መንፈሳዊ ፀጋ እንዲሁም በአበ ነፍሳቸው ፈቃደ ክርስቶስ ምክር የግሸን ደብረ ከርቤን ክብር በመረዳት ፤በ517 ዓ.ም ታቦተ እግዚአብሔር አብንና ታቦተ ማርያምን ከሀገረ ናግራን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት በግሸን አምባ ላይ ቤተ መቅደስ ሠርተው ቀዳሽና አወዳሽ መድበው ደብረዋታል፡፡ በወቅቱም አምባው መግቢያ ካለመኖሩ የተነሣ ተራራውን ሲዞሩ የንብ መንጋ በማየታቸው “አምባ አሰል” ብለውታል፡፡ ትርጓሜውም የማር አምባ ማለት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት አካባቢው አምባ ሰል ሲባል ይኖራል፡፡

በካይሮ አባሲያ ቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል በተደረገው የእጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት በእጩነት ከቀረቡት 3ቱ አባቶች መካከል አንዱን በፓትርያርክነት ለመሾም ዓይኑን በጨርቅ የተሸፈነ ሕፃን እጣውን እንዲያወጣ በማድረግ ብፁዕ አቡነ ታዋድሮስ / ቴዎድሮስ/ የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው ተመርጠዋል፡፡
ሊቀ ጉባዔ ኀይለ ማርያም ንጋቱ ከአባታቸው ከአቶ ንጋቱ ወልደ ሐዋርያትና ከእናታቸው ከወ/ሮ ደመዎዝ ወንድም አየሁ ጥር 12 ቀን 1969 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ በሞረትና ጅሩ ወረዳ ልዩ ስሟ ሽነት ቁስቋም በምትባል መንደር ተወለዱ፡፡ ገና በሕፃን ዕድሜያቸው ወደ ታላቁ ገዳም ወደ ደብረ ጽጌ ማርያም በመሄድ ለአጎታቸው ለአባ ፀጋ ወልደ ሐዋርያ በአደራነት ተስጥተው የቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸውን ትምህርት ሀ ብለው ንባብ ከአባ ሀብተ ማርያም በሚገባ ካጠናቀቁ በኋላ እዛው ገዳሙ ውስጥ ከሚገኙት ከመምህር አፈወርቅ የቃል ትምህርትና ጾም ምዕራፍ በሚገባ ተማሩ እንዲሁም ከታላቁ ሊቅ ከየኔታ ጽጌ ጾመ ድጓና ድጓ ተምርው በመምህርነት ተመርቀዋል፡፡ ቀጥሎም አቋቋምና ዝማሬ መዋሲእት ከየኔታ መስፍን አበበ በሚገባ ተምርው ተመርቀዋል፡፡ ይህን ሁሉ ትምህርት ተምሬያለሁ በቃኝ ሳይሉ ተጨማሪ ቃለ እግዚአብሔር ፍለጋ በ1984 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የካህናት ማሠልጠኛ በመግባት የእውቀት አድማሳቸውን በማስፋት የተክሌ አቋቋምን በመማር በመምህርነት ተመርቀዋል፡፡