በማኅበረ ቅዱሳን የአርባ ምንጭ ማእከል 14ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

ጥቅምት 24 ቀን 2005 ዓ.ም.

ከአርባ ምንጭ ማዕከል


በማኅበረ ቅዱሳን የአርባ ምንጭ ማእከል ከጥቅምት 23-25ቀን 2005 ዓ.ም 14ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ በመካሔድ ላይ ነው ፡፡ በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ ከሀገረ ስብከት የመምሪያ ሓላፊዎች፣ በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የአድባራት አስተዳዳሪዎች እና ሰበካ ጉባኤያት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ፤  የ16 ወረዳ ማእከላት እና 3 ግንኙነት ጣቢያዎች ፤ የ10 ግቢ ጉባኤያት ተወካዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

 

ለሁለት ቀናት በሚቆየው ጉባኤ የማእከሉ የ2004 የሥራ ክንውን ሪፖርትና የ2005 ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የሚያካሂድ ሲሆን በተጨማሪም በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ውይይት ያደርጋል፡፡

 

  • በተለይም ትኩረት የሚደረግባቸው አጀንዳዎች
  1. የአራት ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ አፈፃፀም
  2. የወረዳ ማእከላት እንቅስቃሴ የሚያሳይ የዳሰሳ ጥናት
  3. የአብነት ትምህርት ቤቶችና የአብያተ ክርስትያናት የልማት እንቅስቃሴዎችን ማሳየት
  4. ግቢ ጉባኤያትን ለሐዋርያዊ አገልግሎት ማብቃት

በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የማእከሉ ሰብሳቢ አቶ ገናነው ፍሰሐ ገልጸዋል፡፡