ስርጭቱን ለማስቀጠል ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ተገለጠ፡፡

ጥቅምት 19 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ


በኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቪዥን አማካኝነት ከጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ይሠራጫል በሚል በምእመናን ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የማኅበሩ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር የኢ.ቢ.ኤስ ጣቢያ ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ ሙሉ ሥርጭቱ በመቋረጡ የተነሣ በታሰበው ጊዜ ለመጀመር አልተቻለም፡፡ ሆኖም የኢ.ቢ.ኤስ ሓላፊዎች በገለጹት መሠረት ጣቢያው እንደገና ሥርጨቱን ለማስጀመር ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን ችግሩ እንደተቀረፈም የማኅበሩ ቴሌቪዥን  የሚጀምር መሆኑን አስተባባሪው ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ለዝግጅት ክፍላችን አስታውቀዋል፡፡