የማቴዎስ ወንጌል
ሰኔ 2 ቀን 2006 ዓ.ም
ካለፈው የቀጠለ
-
ይሁዳ የእግዚአብሔር አብ
-
ኤራስ ዓዶሎማዊ የቅዱስ ገብርኤል
-
በግ የእግዚአብሔር ወልድ
ቀለበት፡- የሃይማኖት፤ ባርኔጣ፡- የአክሊለ ሦክ፤ በትር የመስቀል ትዕማር የቤተ አይሁድ፡፡ ትዕማር መያዣ ይዛ ቀረች እንጂ ዋጋዋን እንዳላገኘች ቤተ አይሁድም ትንቢቱን ተስፋውን ሰምተው ቀሩ እንጂ በክርስቶስ አላመኑምና፡፡
ፋሬስ የኦሪት ዛራ የወንጌል ምሳሌ፡፡ ዛራ አስቀድሞ እጁን እንዳወጣ፡፡ ወንጌልም በመልከ ጼዴቅ ታይታ ጠፍታለችና፡፡ ፋሬስ እሱን ወደኋላ ስቦ እንደተወለደ በመካከል ኦሪት ተሠርታለች፡፡ ዛራ በኋላ እንደተወለደ ወንጌል ኋላ ተመሥርታለችና፡፡