የማቴዎስ ወንጌል
ሰኔ 2 ቀን 2006 ዓ.ም
ካለፈው የቀጠለ
-
ይሁዳ የእግዚአብሔር አብ
-
ኤራስ ዓዶሎማዊ የቅዱስ ገብርኤል
-
በግ የእግዚአብሔር ወልድ
ቀለበት፡- የሃይማኖት፤ ባርኔጣ፡- የአክሊለ ሦክ፤ በትር የመስቀል ትዕማር የቤተ አይሁድ፡፡ ትዕማር መያዣ ይዛ ቀረች እንጂ ዋጋዋን እንዳላገኘች ቤተ አይሁድም ትንቢቱን ተስፋውን ሰምተው ቀሩ እንጂ በክርስቶስ አላመኑምና፡፡
ፋሬስ የኦሪት ዛራ የወንጌል ምሳሌ፡፡ ዛራ አስቀድሞ እጁን እንዳወጣ፡፡ ወንጌልም በመልከ ጼዴቅ ታይታ ጠፍታለችና፡፡ ፋሬስ እሱን ወደኋላ ስቦ እንደተወለደ በመካከል ኦሪት ተሠርታለች፡፡ ዛራ በኋላ እንደተወለደ ወንጌል ኋላ ተመሥርታለችና፡፡

ከግንቦት 6 ቀን 2006 ዓ. ም. ጀምሮ ሲካሔድ የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ. ም. መግለጫ በመስጠት ተጠናቋል፡፡ ጉባኤው ሲጠናቀቅ በቀረበው መግለጫም ውሳኔ ሳያገኙ የቀሩ አጀንዳዎችን አካቷል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፡-
የኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዩበልዩ በዓል ግንቦት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ቦሌ በሚገኘው በድርጅቱ ሕንፃ አከበረ፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶችና የድርጅቱ አባላት ተገኝተዋል፡፡
ቀጭን መንገድ ተያያዝነው፡፡ ወንዙ ምን ይባላል አልናቸው ለአንድ አዛውንት “ የማርያም ዥረት ነው የሚባለው” አሉን ፡፡ እንደመቀነት የሚጠማዘዘውን ቀጭን መንገድ እየተከተልን ወደ ዋሻው አፋፍ ደረስን፡፡ ወደ ዋሻው መግቢያ በስተቀኝ በኩል በመጠኑ የጎደጎደ ሥፍራ ይታያል፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅን፡፡ “ከተራራው ሥር እየፈለቀ የሚወርድ ማየገቦ የሚጠራቀምበት ጉድጓድ ነበር፤ (ማየገቦ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ በቦታው ያልነበረው አንድ ዓይና ሌንጊኖስ ከአይሁድ ጋር ለመተባበር ብሎ ኢየሱስ ክርስቶስን በጦር ቢወጋው ውኃና ደም እንደ ለ ፊደል ፈሷል ፡፡ የፈሰሰው ውኃ ማየገቦ ይባላል፡፡) ዋሻው ቤተ መቅደስ ከተደረመሰ በኋላ ደርቋል” አሉን አዛውንቱ፡፡
ቅዱስ እንጦንስ ገዳም (Sankt-Antonius Kloster) በደማቅ ሁኔታ አካሄደ።
“መንፈሰ እግዚአብሔር ያለበት፣ ሰውን ከክፋት፣ ከኃጢአት፣ ከበደል የሚመልስ፤ ይልቁንም ሃይማኖቱን የሚያጸናለት መጽሐፍ ከእግዚአብሔር ነውና ይጠቅማል” በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረው ቃል ነው፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ቃል ያስተላለፈው ለጊዜው በሃይማኖት ትምህርት ወልዶ ላሳደገው ለደቀመዝሙሩ ጢሞቴዎስ ቢኾንም ፍጻሜው ግን እስከ ሕልፈተ ዓለም ለሚነሡ ክርስቲያኖች ሁሉ የተናገረው ነው፡፡ “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።” (፪ኛ. ጢሞ.፫፥፲፮-፲፯)