Entries by Mahibere Kidusan

«ለራሱ ገንዘብ የሚያመቻች በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ባለጠጋ ያልሆነ ሰው እንዲህ ነው»

ሦስተኛ እሑድ

 

 /ሉቃ. 12.21/

ጌታችን በይሁዳ አካባቢዎች እየተዘዋወረ ሲያስተምር ከህዝቡ አንድ ሰው ቀርቦ፡- «መምህር ሆይ ርስቱን ከእኔ ጋር እንዲካፈል ለወንድሜ ንገረው» አለው፡፡ ጌታችን ግን ወደዚህ ምድር የመጣው፣ ለመለኮታዊ /ሰማያዊ/ ዓላማና የሰውን ልጆች ለማዳን እንጂ በሰዎች ምድራዊ ኑሮ ገብቶ ሃብትን ለማከፋፈል ባለመሆኑ፣ ዳግመኛም እርሱ የመጣው ራስን ለሰው መስጠትን፣ ፍቅርንና አንድ መሆንን የምትሰብከውን ወንጌልን ለመስራት በመሆኑ «አንተ ሰው ፈራጅና አካፋይ እንዲሆን በላያችሁ ማን ሾመኝ?» በማለት ይህንን ሊያደርግ እንደማይወድ ከተናገረ በኋላ አጋጣሚውን በመጠቀም አብረውት ለነበሩት እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፤ «የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፤ ከመጎመጀትም ሁሉ ተጠበቁ»፡፡

ጾመ ነቢያት

ዘመኑ ጾመ ነቢያት የተባለበት ምክንያት ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለ ተፈጸመበት እንዲሁም በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምሥጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ የረቀቀው ገዝፎ እየተመለከቱ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ስለ ጾሙ ስለ ጸለዩ ነው፡፡ ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ፣ ወደ ግብፅ ስለ መሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቅ፣ በትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ትንሣኤው፣ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፤ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው «አንሥእ ኃይለከ፣ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሳ እጅህንም ላክ» እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡

የድንግል ማርያም ስሞች

ከመንግስተአብ
 
ስም ለፈጣሪም ሆነ ለፍጡራን ለመጠሪያነት ያገለግላል፡፡ ይህም ስም አንዱን ከሌላው ለይቶ የሚያሳውቅ የፍቅር መግለጫ ነው፡፡ በጽሑፍም ሆነ በቃል ማስተላለፍ የሚቻለው በስም አማካኝነት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ለሚወዳቸውና ለመረጣቸው ሰዎች ስም ያወጣ እንደ ነበር ሁሉ፤ ሰዎችም ያወጡ መጠሪያ ይሰጡ ነበር፡፡ ይህም ስም የሚሰየመው ወይም መጠሪያ ሆኖ የሚሰጠው እንዲሁ በዘፈቀደ ሳይሆን መሠረታዊ ምሥጢርና ትርጉም አለው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን «እስመ ስሙ ይመርህ ኀበ ግብሩ» በማለት ስም ግብርን ሁኔታን እንደሚገልጽ መሥክረዋል፡፡
St.Mary.jpg

ቅዱስ ሲኖዶስ ሦስት መምሪያዎች በሊቃነ ጳጳሳት እንዲመሩ ውሳኔ ሰጠ

በሻምበል ጥላሁን

በሰኖዶሱ አባላት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በሰላም መፈታቱንም ገለጸ

ከጥቅምት 12 እስከ 19/ 2002 ዓ.ም መደበኛ ስብሰባውን ያደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደረጃ መምሪያን ጨምሮ ሌሎች ሁለት መምሪያዎችን በበላይ የሚመሩ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳትን በመምረጥና 10 ነጥቦችን የያዘ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠ ናቀቀ፡፡

Sinod.JPG

የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡቦንግና የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተጠመቁ

በ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የተገነባው ቤተክርስቲያን ተመረቀ፡፡                  

በተከስተ አዳፍራቸው

የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርን ጨምሮ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነርና የካቢኔ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሓላፊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን እምነት ተቀብለው ተጠመቁ፡፡ በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በአንድ ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የደብረ መድኃኒት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ተጠናቆ ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል፡፡Gambela_1.JPG

የመከሩ መሰብሰቢያ ጊዜው አሁን ነው

ለሁሉም ጊዜ አለው እንዳለ ጠቢቡ የሚሠራበትም ሆነ መሥራት የሚቻልበት ጊዜ አለው፡፡ ነገሮች ሁሉ የሚከናወኑበት፣ ቀና የሚሆኑበት፣ የሰው ልቡና ለበጎ ነገር የሚነሣሣበት ያለሙት የሚሠምርበት የዘሩት፣ የተከሉት ሁሉ የሚያፈሩበትና የሚጸድቅበት ጊዜ አለ፡፡

«በህልምም ተረድቶ ወደገሊላ ሀገር ሄደ፤……. ናዝሬት ወደምትባልም ከተማ መጥቶ ኖረ»

ሕዳር 6 ቀን እመቤታችን ጌታን ይዛ ከግብጽ /ከስደት/ ወደ ኢየሩሳሌም መመለሷ ይታሰባል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቀጥሎ ካለው የማቴዎስ ወንጌል ምንባብ በመነሳት ይህንን አስመልክቶ በማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜው ላይ ያስተማረውን ትምህርት እናቀርባለን፡፡