Entries by Mahibere Kidusan

ዕረፍተ አቡነ ሀብተ ማርያም

በተከበረች በኅዳር ፳፮ ቀን ንዑድ ክቡር ንጹሕ መነኰስ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት የትውልድ ሀገሩ የራውዕይ በምትባል በስተ ምሥራቅ ባለች ሀገር ውስጥ ሲሆን በዚያም ስሙ ፍሬ ቡሩክ የሚባል አንድ ደግ ሰው ነበረ። ይህም ከክቡራን ሰዎች ወገን የሆነ ሰው እጅግ ሀብታምም የነበረ ሲሆን በሕጋዊ ጋብቻ ያጋቡት ቡርክት የሆነች ስሟ ዮስቴና የምትባል ሚስት ነበረችው። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች ናት። ይህችውም ደግ እናታችን በሕግ ተወስና ሳለች በጽኑዕ ገድል፣ በጾም በጸሎት በምጽዋትና በስገድትም ትጋደል ነበር።…

ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ

የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፤ አባቱንኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፤ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ ‹መርቆሬዎስ› ማለትም የአብ ወዳጅ ማለት ነው፤ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡

ዕግትዋ ለጽዮን

ያች ያማረ ወርቅን የተጫማች

እንደአጥቢያ ጨረቃ ብርሃን የተመላች

ለክረምቱ ስደት መጠለያ ሆነች

ጽዮንን ክበቧት ሰማይ ታደርሳለች!

በጎ ኅሊና

በዓለም የምናያቸው መልካምም ሆኑ ክፉ ነገሮች ሁሉ መነሻቸው ሐሳብ መሆኑን ስናስተውል ኅሊና ምን ያህል ታላቅ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ኅሊና የሚለው ቃል ‹ሐሳብ፣ ምኞት፣ ከልብ የሚመነጭ ሐሳብ› ማለት ነውና፡፡ በሰው ልጆችም የአእምሮ ሥራ ሂደት ውስጥ ሐሳብ ሲደጋገም ወደ አመለካከት፣ ከሐሳብ የተነሣ አመለካከት ሲያድግም ክፉ ወይም በጎ ወደ ሆነ ማመን፣ አንድ ሰው ከሐሳቡ ወደ ማመኑ የደረሰበት መንገድም ማንነቱን እንደሚወስኑት ባለሙያዎች ያስተምሩናል፡፡ ከሐሳባችን ተነሥቶ ወደ ማንነታችን የደረሰ ነገርም ፍጻሜያችንን ይወስነዋል፡፡…

ጾመ ነቢያት

ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነውን ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ጀምሮ እስከ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ድረስ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃዱ እንጾማለን!

ጾም

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡ ባላችሁበት ሆናችሁ ትምህርታችሁን  በጥሞና ተከታተሉ!
ልጆች! ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው ትምህርት ስለ ጾም ነው፡፡ በመጀመሪያ ጾም ምን ማለት እንደሆነ እና እናንተ ሕፃናት ከሰባት ዓመት ዕድሜያችሁ ጀምሮ እንዴት መጾም እንዳለባችሁ እናስተምራችኋለን፡፡

የግሥ ዝርዝር በመራሕያን

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ትምህርታችን ዐሥሩ መራሕያን አይተን ነበር፡፡ በዚያም መሠረት ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ግሦችን በመራሕያን እንዴት መዘርዘር እንደምችል በዚህ ሳምንት ትምህርታችን አዘጋጅተን አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የትምህርት ክፍለ ጊዜ ይሁንላችሁ!

ዕረፍተ ቅድስት ሐና

ቅድስት ሐና የትውልድ ሐረጓ ከአብርሃም ዘር ነው፡፡ አብርሃም ይስሐቅን፣ ይስሐቅ ያዕቅብን፣ ያዕቆብ ደግሞ ሌዊንና ዐሥራ አንድ ወንድሞቹን ወለዱ፡፡ ከዚህም በኋላ ሌዊ ቀዓትን፣ ቀዓት እንበረምን፣እንበረም አሮን ካህኑን ወለዱ፡፡ ቅዱስ አሮን አልዓዛርን፣ አልዓዛር ፊንሐስን እንዲህም እያለ እስከ ቴክታና በጥርቃ ይወርዳል፡፡…

በዓለ ደብረ ቊስቋም

ደብረ ቊስቋም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወደደ ልጇ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመግደል ከሚፈልጉት ሸሽተው መጠጊያ ያገኙበት እንዲሁም ቅዱስ ገብርኤል ንጉሥ ሄሮድስ መሞቱን ለቅዱስ ዮሴፍ በሕልሙ የገለጸበት ስፍራ ነው፡፡ ‹‹የሕፃኑን ነፍስ የሚሹ ሞተዋልና፥ ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል ሀገር ሂድ›› እንዲል። (ማቴ.፪፥፲፱-፳)