መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የሚዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1043 entries already.
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የሚዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!
የክርስቲያን ወገኖች ሁሉ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ፡፡ መታሰቢያዋን ለሚያደርግ፣ ስሟን ለሚጠራ፣ ለድኆችና ለችግረኞች እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ድረስ ለሚሰጥ የክብር ባለቤት ከሆነ ልጇ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ቃል ኪዳን ተቀብላለችና፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንጉሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…እናንት ልጆች የአባትን ተግሣጽ ስሙ፤ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ›› (መዝ.፬፥፩) በማለት እንደተናገረው የአባቶቻችሁን ተግሣጽ (ምክርና ቁጣ) ሰምታችሁ፣ በእግዚአብሔር ጥበቃ ከትላንት ዛሬ የደረሳችሁ ልጆች! ለዚህ ያደረሰንን እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ታሪክ ስለ እመቤታችን ቃል ኪዳን ነው፤ ቃል ኪዳን ማለት ‹‹ውል ወይም ስምምነት›› ማለት ነው፤ እግዚአብሔር ከአባቶቻችን ጋር በተለያየ ጊዜ ቃል ኪዳንን ገብቷል፤ እንደ ትእዛዙ ለሚኖሩ የሚፈልጉትን ሊያደርግላቸው ቃል ኪዳንን ሰጥቷቸዋል፤ በነቢዩ ሕዝቅኤል ‹‹የሰላምም ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር አደርጋለሁ፤ ዘለዓለም ቃል ኪዳን ይሆንላቸዋል፤ እኔም እባርካቸዋለሁ፤ አበዛቸውማለሁ፤ መቅደሴንም ለዘለዓለም በመካከላቸው አኖራለሁ…›› (ሕዝ.፴፯፥፳፮) በማለት ነግሮናል፡፡
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን ስለ ዐበይት አናቅጽ እና ዐሥራው አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና የ ‹‹ሀ፣ አ፣ ወ እና የ›› የሚያመጡት የርባታ ለውጥ በግሥ ርባታ እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
እፎ ኃደርክሙ…
ተናገረው ይውጣ እንጂ አንደበትህ አይዘጋ
የአባቶችህ መገለጫ ዜማቸውን አትዘንጋ
ሰዎች በሕይወት ዘመናችን ውስጥ በሁለት ነገሮች ታጥረን እንጸልያለን፤ እንሠራለን፤ እንኖራለን፡፡ ሁለቱ ነገሮችም እኛ የምንፈልጋቸውና የሚያስፈልጉን ናቸው፡፡ እነርሱንም ይዘን ከእግዚአብሔር ፊት በመቆም የሚያስፈልገንን ነገር እንጠይቀዋለን፡፡ ነገር ግን የፈለግነውን ወይም የጠየቅነውን ሁሉ ሳይሆን የሚያስፈልገንን አምላካችን ለእኛ ያደርግልናል፤ ወይም ይሰጠናል፡፡
ነነዌ የሜሶፖታምያ ከተሞች ከሆኑት መካከል አንዷ ናት፡፡ ከሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ ፫፻፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደ ነበረች በታረክ ይነገራል፡፡ በ፵፻ (ዐራት ሺህ) ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በናምሩድ በኩል ከተቆረቆረችም በኋላ በ፲፻፬፻ (አንድ ሺህ ዐራት መቶ) ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የአሦራውያን ዋና ከተማ ሆናለች፡፡ (ዘፍ.፲፥፲፩፣፪ኛነገ.፲፱፥፴፮)
በከተማዋም ታዋቂ የነበረ አስታሮት የተባለ የጣዖት ቤተ ነበረ፡፡ በዚህች ከተማ የሚኖሩት ሰዎች የሚሠሩት ክፋትና ኃጢአት እጅግ ከመብዛቱ የተነሣ ጽዋው ሞልቶ መጥፊያቸው ስለ ደረሰ ለፍጥረቱ ርኅራኄ ያለው እግዚአብሔር ግን ንስሓ ይገቡ ዘንድ ነቢዩ ዮናስን ልኮላቸዋል፡፡ ይህ ነቢይ ከአሕዛብ ወደ አሕዛብ ወደ ንስሓ ይጠራቸው ዘንድ ነበር የተላከ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ነቢይ ኢሳይያስ በዚያን ዘመን ይኖሩ ለነበሩት እስራኤላውያን እንዲናገር በታዘዘው መሠረት ይህን ቃል ነገራቸው፤ ‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ፡፡›› (ኢሳ.፷፮፥፲፫) ከነበሩበት መከራና ከጭንቀታችው ሁሉ እንደሚያጽናናቸው እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አማካኝነት ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ይህ ቃል በዚያን ዘመን ላለው ሕዝብ ብቻ የሚያልፍ ሳይሆን ዛሬ ያለነውም ትውልድ በተለይም እኛ ልናስተውለው የሚገባ ቃል ነው፡፡
በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከሞተ በኋላ ወደ በረሃ ሄደ፡፡ ሕዝቡም ሰምቶ ተከተለው፡፡ በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሕዝቡን እንዲያሰናብት ጠየቁት፡፡ ይህም ለዚያ ሁሉ ሕዝብ የሚሆን ምግብ ስለሌለ የሚበሉትን እንዲገዙ ነበር፡፡ እርሱ ግን ለጊዜው የተገኘውን አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ ባርኮ ሁሉንም እስኪጠግቡ ድረስ መገባቸው፡፡ ተርፎም አሥራ ሁለት መሶብ ተነሣ፡፡ የተመገቡትም ሕዝብ ሴቶችና ሕፃናት ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ ወንዶች ነበሩ፡፡ ‹‹አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ የበሉትም ወንዶች አምስት ሺህ ነበሩ›› እንዲል፤ ሴቶቹ ያልተቆጠሩበት ምክንያት በዐደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው፤ ሕፃናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ስለሚበዛ ነው፡፡ (ማር.፮፥፵፬)
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን ስለ አዕማድ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና አምስቱ አዕማድን እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
