ቃላተ አንጋር
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በዘመነ ሉቃስ የመስከረም ወር ሁለተኛ ክፍለ ጊዜያችን የሆነውን ትምህርት ከማቅረባችን በፊት በባለፈው ትምህርታችን በግእዝ ቋንቋ የምንጠቀምባቸውን ዓረፍተ ነገሮች ከቤተሰቦቻችሁ፣ ከዘመዶቻችሁ፣ ከጓደኞቻችሁ እንዲሁም ከጎረቤቶቻችሁ ጋር እንድትለማመዷቸው አቅርበንላችሁ እንደነበር በማስታወስ በሚገባ ተረድታችሁ እንደተለማመዳችሁትና በቃላችሁ እንደያዛችኋቸውም ተስፋ እናደርጋለን!
የዚህ ሳምንት ትምህርታችን ደግሞ በግእዝ ቋንቋ ውስጥ የምንጠቀምባቸው የንግግር ስልቶች (ቃላተ አንጋር) ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ስለዚህም በመጀመሪያ በግእዝ ቀጥሎም በአማርኛ ስልቶቹን አከታትለን አቅርበንላችኋልና ተከታተሉን!