Entries by Mahibere Kidusan

ዕውቀት ሥጋዊ ወመንፈሳዊ

ዕውቀት ‹ዖቀ› ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው፤ ትርጓሜውም ‹ዐወቀ› ወይም አንድን ነገር በአግባቡ መረዳትንና መገንዘብን እንዲሁም አንድን ነገር ለመፈጸምና ለማከናወን  የሚያስችለንን ችሎታ የሚገልጽ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ዕውቀት አንድን ችግር ለማስወገድ የሚያስችል አቅም ወይም ችሎታ መሆኑ ይታመናል፡፡  በግሪኩ ግኖስ የሚል ትርጉም ያለው ሲሆን ዕውቀትን የሁሉም ነገር መፍቻ ቁልፍ አድርጎ የመመልከት ዝንባሌም ያለው ሲሆን ሰው በዕውቀቱ የዘለዓለም ሕይወትን ድኅነትን እንደሚያገኝ በግኖስቲኮች ዘንድ ይታመናል፡፡ በአንጻሩ ዕውቀት የላቸውም ተብለው የሚታሰቡ ሰዎች አላዋቂዎች ወይም አግኖስ ተብለው የሚጠሩ ሲሆን እነዚህ አካት ያልበራላቸው በጨለማ ውስጥ ያሉ እንደሆነ በግሪክና በሮማ ሥልጣኔ ዘመን ይታመን እንደነበር እንገነዘባለን፡፡

ሲመቱ ለሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕታት ቅዱስ እስጢፋኖስ

የስሙ ትርጓሜ ‹አክሊል› የሆነው በሕገ ወንጌል የመጀመሪያ ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳማዊ ሰማዕት የተባለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ‹‹ሊቀ ዲያቆናት›› ከመባሉ በፊትም በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነበር፤ ከዚያም ዲያቆን ሆኖ ተሾሟል፤ ይህም ጥቅምት ፲፯ ቀን ነው፡፡

ዕረፍቱ ለሊቀ ጳጳስ አባ ድሜጥሮስ

ቅዱስ ድሜጥሮስ የእስክንድርያ ዐሥራ ሁለተኛ ጳጳስ ከመሆኑ በፊት የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያልነበረው በግብርና ሥራ የሚተዳደር ሰው ነበር፡፡አባቱ ደማስቆ ወይም እንድራኒቆስ አጎቱ ደግሞ አርማስቆስ ወይም አስተራኒቆስ ይባላሉ፡፡ ሁለቱም በዘመነ ሰማዕታት ከኢየሩሳሌም ርቀው በባዕድ ሀገር በፋርስ ባቢሎን በስደት ለረጅም ዘመናት ይኖሩ ነበር፡፡ በዚህ የስደት ዘመናቸው ከሁለቱ (ደማስቆና አርማስቆስ) በስተቀር በሀገሩ የሚኖሩት አሕዛብ ነበሩ፡፡…

አኀዝ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የግእዝ ቋንቋን ለመማር ይረዳችሁ ዘንድ በየሁለት ሳምንቱ እያዘጋጀን የምናቀርብላችሁ ‹‹የግእዝ ይማሩ›› ዐምድ የዝግጅት ክፍሉ ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ለተወሰኑ ጊዜያት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በአዲስ መልክ ለአንባብያን በሚያመች መንገድ አዘጋጅተን አቅርበንላችኋልና በጥሞና ተከታተሉን፡፡

ልጆች ዘወትር ጸልዩ!

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡

ልጆች የዛሬ ትምህርታችን ስለጸሎት ነው፤ በመጀመሪያም የቃሉን ትርጉም እንመልከት፡፡…

ክብረ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩትና በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ ፻ (መቶ) ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዕረፍታቸው እንዲሁም ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ዕለት በሀገራችን ኢትዮጵያ በድምቀት ይከበራል፡፡

‹‹አንደበትህን ከክፉ ከልክል›› (መዝ.፴፫፥፲፫)

ሰዎች አንደበታችንን እግዚአብሔርን ለማመስገንና በጎ ነገርን ለመናገር ልንጠቀመው ይገባል። በእያንዳንዱ ንግግራችን የምናወጣቸው ቃላትም ሆነ የምንመሠርታቸው ዓረፍተ ነገሮች ከክፋት የጸዱ መሆን አለባቸው። ለዚህም ነው ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ›› በማለት የተናገረው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በጾመ ድጓው ሲናገር ‹‹ይጹም ዐይን ይጹም ልሳን እዝንኒ ይጹም እምሰሚዐ ሕሡም፥ ዐይን ይጹም፣ አንደበትም ይጹም፣ ዦሮም ክፉን ከመስማት ይጹም›› ብሎ እንደተናገረ አንደበት በቃለ እግዚአብሔር እና በበጎ መንፈሳዊ ምግባራት ካልተገታችና ካልታረመች የሰውን ልጅ ወደ ጥልቅ የበደልና የጥፋት መንገድ ሊጥሉት ከሚችሉ ሕዋሳት አንዲቱ ናት። (መዝ.፴፫ (፴፬)፥፲፫)

‹‹ለነገ አትጨነቁ፤ ነገ ለራስዋ ታስባለችና›› (ማቴ.፮፥፴፬)

ጭንቀት እንደ የማኅበረሰቡ አኗኗርና የኑሮ ፍልስፍና የሚሰጠው ትርጉም ከቦታ ቦታና ከሰው ሰው ይለያያል። የሕዝቦቻቸው መሠረታዊ ፍላጎቶች ባልተሟሉባቸው አንዳንድ ሀገራት ምጣኔ-ሀብታዊ አለመረጋጋት በብዛት የሚስተዋል የጭንቀት መንሥኤ ነው። በአንጻሩ ብዙዎቹ ዜጎቻቸው የቅንጦት ሕይወት በሚመሩባቸው ‹ሥልጡን› ሀገራት ደግሞ፥ ደስታ ይገኝባቸዋል ተብለው የሚጀምሩ የዝሙት፣ የሱስ፣ የዘፈን… የመሳሰሉት እኩይ ተግባራት ከጊዜያት በኋላ እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚቃትተውና እውነተኛ ደስታ ምን ማለት እንደሆነ አንጠርጥሮ በሚያውቀው ውሳጣዊ ኅሊናቸው ዕረፍት የለሽ ሙግት የተነሣ ደስታ ሰጪነታቸው አብቅቶ መዳረሻቸው ጭንቀት ይሆናል። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ለዚህ ኅሊናዊ ምሪት የሚሰጡት መልስ በአብዛኛው አሁንም ተቃራኒውን መሆኑ ነው። ‹‹ለምንድነው የምኖረው?›› ለሚለው ጥያቄያቸው መልሳቸው ‹‹ለምንም!›› የሚል ይሆንና የሕይወታቸውን ፍጻሜ ያበላሸዋል።…