የጽጌ ወር
ምድር በአበቦችና በዕፅዋቶች ተሞልታ የምታሸበርቅበት ወቅት የጽጌ ወር በክርስቲያናዊ ሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ የመዳኛችን ተስፋ የሆነችውና የዓለምን ቤዛ የወለደችን ቅድስት ድንግል ማርያም አበባውን በሚያስገኙት ዕፀዋትና በምድር፣ የተወደደ ልጇ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ በአበባው እንደሚመሰሉ ቀደምት ነቢያት አስተምረውናል፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 978 entries already.
ምድር በአበቦችና በዕፅዋቶች ተሞልታ የምታሸበርቅበት ወቅት የጽጌ ወር በክርስቲያናዊ ሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ የመዳኛችን ተስፋ የሆነችውና የዓለምን ቤዛ የወለደችን ቅድስት ድንግል ማርያም አበባውን በሚያስገኙት ዕፀዋትና በምድር፣ የተወደደ ልጇ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ በአበባው እንደሚመሰሉ ቀደምት ነቢያት አስተምረውናል፡፡
በሀገራችን ኢትዮጵያ በወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ የሚገኘው ታላቁ የግሸን ማርያም ደብር የግማደ መስቀሉ መገኛ በመሆኑ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ትልቅ ተስፋና መመኪያ ነው፡፡ መስቀል የክርስትናችን መገለጫ፣ የብርሃናችን ዐምድ እንዲሁም የሰላማችን መገኛ ነውና፡፡
ጉባኤ ኒቅያ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷን የጠበቀችበት፣ አርዮስና አርዮሳውያን የተወገዙበት፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት፣ አዳኝነት፣ ጌትነት፣ መድኃኒትነት የተመሠከረበት፣ ኦርቶዶክስ የሚለው ስም ትምክህት የሆነበት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ይህን ጉባኤ ትቀበላለች፤ ትልቅም ስፍራ አላት፡፡
እስኪ እንጀምር ከልደቷ
በፍጥረቱ በውልደቷ
ከቀን በዐራተኛ መገኘቷ
በረቡዕ በዐራተኛ
ከተራራ ከፍ ያለች ከፀሐይ መለስተኛ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ አሸጋግሮ በሰላም ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! ዕንቁጣጣሽ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን እሙን ነው፡። መልካም! የአዲስ ዓመት ትምህርት ለመጀመር እንዴት እየተዘጋጃችሁ ነው? ባለፈው ዓመት በትምህርታችን ደከም ያለ ውጤት አስመዝግበን የነበርን ዘንድሮ በርትተን በመማር በጥሩ ውጤት ከክፍል ክፍል ለመሻገር ከአሁኑ ማቀድና መበርታት አለብን፡፡ እንዲሁም ደግሞ ለአገርና ለቤተ ክርስቲያን እየጸለይን የሰላምን ዘመን ተስፋ እናድርግ! መልካም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት ለእናንተ ያስተምራሉ በማለት በጻፍንላችሁ በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? አሁን ደግሞ ስለ ቅዱስ መስቀሉ በዓል ጥቂት ልናካፍላችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!
ሕዝበ ክርስቲያን ከሚያከብሩት ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ጼዴንያ ማርያም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በመስከረም ፲ ቀን ይከበራል፡፡ በተለይም በሀገራችን ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ቡራዮ አካባቢ ጼዴንያ ማርያም በምትባል ቤተ ክርስቲያን በዕለቱ ታቦተ ክብሩ ከመንበሩ ወጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል፡፡ ጼዴንያ በምትባል ሀገር ሥጋ የለበሰች ከምትመስል ሥዕል ከሠሌዳዋ ቅባት እየተንጠፈጠፈ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ተአምር ተገልጧልና፤ ይህችን ድንቅ ሥዕልም ቅዱስ ሉቃስ እንደሣላት ይነገራል።
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! እንኳን ለዘመነ ሉቃስ አደረሳችሁ! እግዚአብሔር አምላክ አዲሱን ዓመት የሰላምና የደስታ እንዲያደርግላችሁ ከወዲሁ እንመኝላችኋለን!
አዲሱ ዓመት ቤተሰቦቻችንን፣ ዘመዶቻችንን፣ ጓደኞቻችንን እንዲሁም ጎረቤቶቻችንን የምንጠይቅበትና እንኳን አደረሳችሁ የምንልበት ጊዜ ነውና ከሰዎች ጋር ንግግር የምናደርግባቸው የመግባቢያ ዓረፍተ ነገሮች በግእዝ ምን እንደሆኑ ታውቁ ዘንድ እንደ ዐውደ ዓመት ስጦታ እነሆ ብለናችኋል!
የምሕረት አምላክ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ኃጢአት በደላችንን ሁሉ ታግሦ እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ለአዲሱ ዓመት አበቃን፡፡ ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍስሐ ያደለን አምላካችን በሰጠን የተፈጥሮ ጸጋ ተጠቅመን ከክፉ መንገዳችን እንድመልስ፣ ከኃጢአት እንድንነጻ እንዲሁም በጎ ሥራ እንድሠራ ነው፡፡ ምሕረቱ የበዛ ቁጣውም የራቀ ቸርነቱ አያልቅምና በእርሱ ጥላ ሥር ተጠልለን በሥነ ምግባር እንድንኖር መልካም ፈቃዱ ሆነ፡፡ ይህንንም በቅዱሳን ልጆቹ ላይ ፈጽሞ አሳይቶናል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ክርስቲያን የተባልን በሙሉም ምሕረትን ስለማድረግ ልናውቅ ያገባናል፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሕረት በሁለት እንድሚከፈል ያስተምሩናል፤ እነርሱም ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ ናቸው፡፡
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ በረከት!
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት መስከረም ሁለት የተከበረ ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጥምቁን ክብር ‹‹እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም” በማለት መሥክሮለታል፡፡ (ማቴ. ፲፩፥፲፩፣ ሉቃ ፯፥፳፰)