Entries by Mahibere Kidusan

ስብከተ ወንጌል

ቅዱስ ዳዊት “ኢትዝክር ለነ አበሳነ ዘትካት ፍጡነ ይርከበነ ሣህልከ እግዚኦ እስመ ተመንደብነ ፈድፋደ፤ የቀደመውን በደላችንን አታስብብን፥ ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና”  እንዳለ  የቀደመ በደላችንን ሳያስብብን ጭንቀታችንን ችግራችንን ይቅር ብሎ ወደ እዚህ ምድር መጥቶ የምሥራች፣ ብርሃን፣ መንገድ፣ መስታወት፣ የሕይወት ዛፍ የሆነችውን ወንጌልን ሰበከን፤ አስተማረን። (መዝ.፸፰፥፰) ሐዋርያትንም “ሑሩ ውሰተ ኩሉ ዓለም ወስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት፤ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ” በማለት በይሁዳ፣ በኢየሩሳሌም፣ በሰማርያና እስከ ዓለም ዳርቻ እንዲያስተምሩ ላካቸው። (ማር.፲፮፥፲፭)

‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ ያድናቸውማል›› (መዝ.፴፫፥፯)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? ደጋግመን ስለ ትምህርታችሁ የምንጠይቃችሁ በዚህ ጊዜ የእናንተ ተቀዳሚ ተግባራችሁ መሆን ያለበት እርሱ ስለሆነ ነው፡፡ መማርና ማወቅ ብልህና አስተዋይ ያደርጋል፤ ታዲያ ስትማሩም ለማወቅ እና መልካም ሰው ለመሆን መሆን አለበት! ደግሞም የዓመቱ አጋማሽ ፈተናም እየደረሰ በመሆኑ በርትታችሁ ማጥናታችሁ መምህራን የሚያወጡትን ጥያቄ ለመመለስ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ ጥያቄውን ከመመለስ በተጨማሪ ምን ያህል እውቀት እንዳገኛሁ ልታውቁበት ይገባል!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ታሪክ በታኅሣሥ ፲፱ ቀን ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ስለሚከበርለት ቅዱስ ገብርኤልና ስላዳናቸው ሦስቱ ሕፃናት ነው፡፡

“በምንም አትጨነቁ” (ፊል.፬፥፮)

በሕይወታችን ለሚገጥመን ማንኛውም ችግር ከእግዚአብሔር ዘንድ መፍትሔ ይኖረዋል፡፡ በእርሱ አምነንና ታምነን እስከኖርን ድረስ ከመከራና ከሥቃይ ያወጣናል፡፡ ሰዎች በተለያዩ ጊዜያት በሕይወታቸው ውስጥ ችግር ሊገጥማቸው ይችላል፡፡ የሚረዳቸው ቤተሰብም ሆነ ዘመድ ከሌላቸው ደግሞ ችግራቸውን ስለሚያባብሰው ወደከፋ መከራ ውስጥ ሲገቡ ሰምተንም ሆነ ተመልክተን ይሆናል፡፡ ነገር ግን አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን የሚፈትነው ለበጎ እንደሆነ በማወቅና በመረዳት የነገን ተስፋ አድርጎ መኖር ይኖርብናል እንጂ ተስፋ መቁርጥ ወይም ማማረር አይገባም፡፡ በተቻለው መጠን ለኑሯችን ተሯሩጠን የዕለት ጉርሻችን መሙላት እንዲሁም ወደ ተሻለ ሕይወት መትጋት ይገባል፡፡

ሥርዓተ አምልኮ

ሥርዓት  “ሠርዐ” ሠራ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ደንብ፣ አሠራር፣ መርሐ ግብር ማለት ነው። በሃይማኖት ውስጥ የሚፈጸም የመንፈሳዊ አገልግሎትና አሠራር እንዲሁም ክርስቲያናዊ ሥርዓትን ያመለክታል።

 ሥርዓተ አምልኮት

የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮት ለአምላካችን እግዚአብሔር የሚቀርብ ሥርዓት ነው፡፡ ይህም ሥርዓተ ጸሎትን፣ ሥርዓተ ጾምን፣ ሥርዓተ ምጽዋት፣ ሥርዓተ ስግደትን፣ ሥርዓተ በዓላትን፣ ሥዕላትን፣ መስቀልንና ንዋያተ ቅድሳትን ያካትታል፡፡

“ለፀሐይም ቀንን አስገዛው፤ ጨረቃንና ከዋክብትንም ሌሊትን አስገዛቸው” (መዝ.፻፴፭፥፰‐፲)

‹‹የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትን ሥራቸውን ዕወቅ፤ ከሁሉ የሚደንቅ ክበባቸውን ከሁሉ የሚበልጥ ብርሃናቸውን ሁሉ ዕወቅ፤ በየወገናቸው የሚያበሩ የሚመላለሱ የእነዚህን የምሳሌያቸውን ሥራ ዕወቅ፤ ሁሉ ጊዜ እርስ በእርሳቸው እንደምንም እንደሚቀራረቡ ዳግመኛም እንደምንም እንደሚራራቁ ዕወቅ…›› (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ባስልዮስ ምዕራፍ ፴፭፥፲፯)

የዕለተ ሠሉስ ፍጥረታት

ዕለተ ማክሰኞ የፍጥረት ሦስተኛ የምስጋና ሁለተኛ ቀን ነች፤ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ደግሞ ዕለተ ቀመር ትባላለች፤ በፀሐይ አቆጣጠር ሰባተኛ ቀን ትባላለች፡፡ ዛሬ ግን የምናነሣው በዕለተ ፍጥረት ስለተከናወነባት ክንዋኔ ነው፡፡

በዓታ ለማርያም

ታኅሣሥ በባተ በሦስተኛው ቀን የሚታሰበውና የሚከበረው በዓል ‹‹በዓታ ለማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ ከእናቷ ከቅድስት ሐና እና ከአባቷ ቅዱስ ኢያቄም በስዕለት የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት የከበረ እንደመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡

‹‹አትስረቅ›› (ዘፀ.፳፥፲፭)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? የመንፈቀ ዓመቱ (የዓመቱ ግማሽ) የትምህርተ ዘመን ሊጠናቀቅ የቀሩት ጥቂት ሳምንታት ናቸው፡፡ ለመሆኑ ምን ያህል ዕውቀት አገኛችሁ? ትናንት የማታውቁት አሁን አዲስ የተጨመረላችሁ ዕውቀት ምንድን ነው? ይህን ራሳችሁን መጠየቅ አለባችሁ? መማራችሁ ከክፍል ወደ ክፍል ለመሸጋገር ብቻ ሳይሆን ባላችሁ ግንዛቤ ላይ ሌላ ዕውቀት ለመጨመር ነውና በርቱ! መማራችሁ ለተሻለ ሕይወት፣ ዛሬን ከትላንትና፣ ነገን ደግሞ ከዛሬ የተሻለ ሆኖ እንድታገኙት ሊሆን ይገባል፡፡ መልካም! ለዛሬ የምንማረው ከዐሥርቱ ትእዛዛት መካከል አንድ ስለሆነው ‹‹አትስረቅ›› ስለሚለው የእግዚአብሔር ሕግ ነው!