ዕረፍቱ ለአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ
የከበረ ገድለኛ አባት የዋልድባው አባ ሳሙኤል የአባቱ ስም እስጢፋኖስ የእናቱ ስም ደግሞ ዓመተ ማርያም ነው። እነርሱም በዘመድ የከበሩ ደጋግ ናቸው፤ እነርሱም በአክሱም ሀገር ሲኖሩ ሁለት ልጆችን ወለዱ። አንደኛው ስሙ ገብረ ክርስቶስ ሲሆን ይህ ሁለተኛው ደግሞ የእግዚአብሔር ሰው አባ ሳሙኤል ነው።
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 806 entries already.
የከበረ ገድለኛ አባት የዋልድባው አባ ሳሙኤል የአባቱ ስም እስጢፋኖስ የእናቱ ስም ደግሞ ዓመተ ማርያም ነው። እነርሱም በዘመድ የከበሩ ደጋግ ናቸው፤ እነርሱም በአክሱም ሀገር ሲኖሩ ሁለት ልጆችን ወለዱ። አንደኛው ስሙ ገብረ ክርስቶስ ሲሆን ይህ ሁለተኛው ደግሞ የእግዚአብሔር ሰው አባ ሳሙኤል ነው።
ቅድስት አርሴማ ከሃያ ሰባቱ ደናግል ጋራ ሰማዕትነት ከተቀበለች በኋላ የቅዱሳን ሰማዕታቱን ዕፅም ፍልሠታቸው በዚህ በቅዱስ ጎርጎርዮስ እንዲደረግ ሆነ፤ ይህም ታኅሣሥ ስድስት ቀን ነው፡፡ እንዲሁ ደግሞ የእርሷ ማኅበርተኞች የሚባሉ የመቶ ዐሥራ ዘጠኝ ሰማዕታት ዝክራቸው ነው። ከዚያም በስሟ ያማረ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው እንዲሁ አከበሩበት።
ዘመነ ስብከት ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፊት ከታኅሣሥ ፯ ጀምሮ እስከ ፳፱ ያለው ወቅት ነው፡፡ ሳምንታቱም ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ ይባላሉ፡፡ በዚህም ወቅት ስለ ጌታችን ኢየሱስ መወለድ ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ይሰበክበታል፡፡
ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተመረጡ የተመረጠች፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተከበሩ የተከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ መቅደስ የገባችበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ‹‹በዓታ ለማርያም›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
ጥበብ ከእግዚአብሔር አምላክ የሚሰጥ፣ ከሁሉ የበለጠና የላቀ የዕውቀት ሥጦታ እንዲሁም ሰማያዊ ርስትን የሚያወርስ መንፈሳዊ ጸጋ ነው፡፡ በሰዎች አእምሮ ውስጥም ማስተዋልን ያጎናጽፋል፡፡ በዚህም ጸጋ የእውነት መንገድን ማወቅና ጽድቅን መሥራት ይቻላል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በምሳሌው እንደተናገረው ‹‹ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፤ ጥበብንም ያበዛል፤ ጽድቅንም አስተምረው ዕውቀትን ያበዛል፡፡›› (ምሳ. ፱፥፱)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለተከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹… እግዚአብሔር ሕፃናትን ይጠብቃል…›› በማለት እንደተናገረው በእግዚአብሔር ጥበቃ በሰላምና በጤና እንደቆያችሁልን ተስፋችን የታመነ ነው፡፡ (መዝ.፻፲፬፥፮)
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ትምህርታችን የግሥ ዝርዝር በዐሥሩ መራሕያን ዓይተን ነበር፡፡ በዚህም ክፍለ ጊዜያችን ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስሞችን በመራሕያን እንዴት መዘርዘር እንደምችል አዘጋጅተን አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የትምህርት ክፍለ ጊዜ ይሁንላችሁ!
በተከበረች በኅዳር ፳፮ ቀን ንዑድ ክቡር ንጹሕ መነኰስ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት የትውልድ ሀገሩ የራውዕይ በምትባል በስተ ምሥራቅ ባለች ሀገር ውስጥ ሲሆን በዚያም ስሙ ፍሬ ቡሩክ የሚባል አንድ ደግ ሰው ነበረ። ይህም ከክቡራን ሰዎች ወገን የሆነ ሰው እጅግ ሀብታምም የነበረ ሲሆን በሕጋዊ ጋብቻ ያጋቡት ቡርክት የሆነች ስሟ ዮስቴና የምትባል ሚስት ነበረችው። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች ናት። ይህችውም ደግ እናታችን በሕግ ተወስና ሳለች በጽኑዕ ገድል፣ በጾም በጸሎት በምጽዋትና በስገድትም ትጋደል ነበር።…
የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፤ አባቱንኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፤ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ ‹መርቆሬዎስ› ማለትም የአብ ወዳጅ ማለት ነው፤ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡
ያች ያማረ ወርቅን የተጫማች
እንደአጥቢያ ጨረቃ ብርሃን የተመላች
ለክረምቱ ስደት መጠለያ ሆነች
ጽዮንን ክበቧት ሰማይ ታደርሳለች!