Entries by Mahibere Kidusan

ሆሣዕና

‹ሆሼዕናህ› ከሚለው በዕብራይስጥ ቃል የተገኘው ‹ሆሣዕና› ትርጉሙ ‹እባክህ አሁን አድን› ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ ‹‹አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡›› (መዝ.፻፲፯፥፳፭-፳፮) የሆሣዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና ሕፃናት ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም›› በማለት ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡ በዓሉም ሆሣዕና የሚለውን ስያሜ ያገኘው በዕለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡ (ዮሐ.፲፪፥፲፫)

ንዑስ አንቀጽና ቅጽሎች

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሦስት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታን እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ በተማራችሁት መሠረት ላቀረብንላችሁ የመልመጃ ጥያቄዎች ምላሻቸውን እንዲሁም ‹ንዑስ አንቀጽና ቅጽሎች› በሚል ርእስ የዛሬውን ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!     

‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› (መዝ.፯፥፱)

ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› በማለት አስተምሯል፡፡ (መዝ.፯፥፱) ከዚህም ቃል እንደምንረዳው አምላካችን የሚሣነው ነገርም ሆነ ከእርሱ የሚሠወረውም ነገር እንደሌለ ነው፡፡ ሁሉንም ሳንነግረው የሚያውቅ አምላክ እንደሆነ ያሰብነውን ብቻም ሳይሆን ገና ያላሰብነውን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡

ኒቆዲሞስ

በግሪክ ቋንቋ ኒቆዲሞስ የሚለው ቃል ትርጓሜ ድል ማድረግን ወይም አሸናፊነትን የሚያመለክት ነው፡፡ በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሚሰብክበት ጊዜ አንድ ፈሪሳዊ ከአይሁድ አለቆችና መምህራን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ ሰው እንደነበረና የጌታችንን ቃል በሌሊት ወደ እርሱ በመሄድ እንደተማረ በወንጌለ ዮሐንስ ተጠቅሷል። (ዮሐ.፩፥፪)

በዓለ ፅንሰት

በተከበረች መጋቢት ፳፱ ቀን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የከበረ መልአክ ገብርኤል የምሥራች የነገረበት ድኅነትን የተመላች ታላቅ በዓል ናት፡፡ በዚህም የከበረ ወንጌል ምስክር ሆኗል፡፡

ዝርዝር ርባታ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሁለት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ የመጨረሻውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ጥንተ ስቅለት

ለዓለም ሁሉ ድኅነት መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት በባተ በ፳፯ኛው ቀን በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ልጆቹም ይህን እናዘክር ዘንድ ዓይን ልቡናችንን ወደ ቀራንዮ እናንሣ!

ገብር ኄር

በጎ አገልጋይ ለጌታው ታምኝ እንደመሆኑ ‹‹ገብር ኄር›› ይባላል፡፡ ይህም ስያሜ ለዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት እንደተሰጠ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይገልጻል፡፡ የስያሜው መነሻ የሚገኘው ደግሞ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው በማቴዎስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)

ጥንተ ሆሣዕና

የዓለም መድኃኒት አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንባባና ልብስ ተነጥፎለት በአህያ ውርንጭላዋ ተጭኖ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት ‹‹ጥንተ ሆሣዕና›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይዘከራል፡፡ ሆሣዕና ማለት ‹‹አሁን አድን›› ማለት ነው፤ (ማሕቶተ ዘመን ገጽ ፻፷)

ደብረ ዘይት

ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኘው ተራራ ደብረ ዘይት የጸሎተ ሐሙስ ማታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘበት ነው፡፡ ቤተ ፋጌ እና ቢታንያ በኮረብታው ጫፍ እና በምሥራቅ ዳገት ላይ ይገኛሉ። ጌታችን ኢየሱስ ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ ተናገሯል።