Entries by Mahibere Kidusan

‹‹ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊትም ጾመ›› (ማቴ.፬፥፪)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የመንፈቀ ዓመቱ ትምህርት ተጠናቆ ፈተና ተፈትናችሁ ጥሩ ውጤት እንዳመጣችሁ ተስፋችን ነው፤ በርቱ!
ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ ዐቢይ ጾም ነው፤ ዐቢይ ማለት ታላቅ ማለት ነው፤ አባቶቻችን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት ከሰባት ዓመት በላይ የሆኑ ክርስቲያኖች ሁሉ እንዲጾማቸው የታወጁ ሰባት አጽዋማት አሉ፤ ከእነዚህ መካከል ደግሞ አንዱ ዐቢይ ጾም ነው::

ፈቃደ እግዚአብሔር

በሰዎች ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር ክቡር ፍቃድ አለ፤ እነዚህም ሁለት ፍቃዳት ናቸው፡፡ አንደኛው ግልጽ ፈቃድ ሲባል ሁለተኛው ደግሞ ስውር ፈቃድ ይባላል፡፡ ግልጽ ፍቃዳት የሚባሉት በመጽሐፍ ተጽፈው የምናነባቸው ናቸው፤ በሕግ መልክ በብሉይ እና በሐዲስ ኪዳን የተቀመጡልን ትእዛዛቱ እንድንሰማቸው፣ እንድንማራቸው፣ እንድንኖራቸው የተሰጡትን ነው፡፡ መጽናናትን፣መረጋጋትን ገንዘብ የምንዳርባቸው፣ ተግሣጽንና ምክርን የምንሸምትባቸው ገባያችን ናቸው፡፡

ዘወረደ

ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሣት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ ‹‹አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም›› ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት ዋዜማ፣ መግቢያ (መሐትው) ሆኖ ከዋዜማ በፊት ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፤ ይዘመራል፤ ይመሰገናል ማለት ነው፡፡

ዐቢይ ጾም

‹ዐቢይ›› የተባለው የዓለማት ፈጣሪ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአርአያነት ጾሞ የመሠረተው ጾም ስለሆነ ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ካሉት ሰባት የአዋጅ አጽዋማት ረጅሙ (፶፭ ቀን ያለው) ስለሆነ ደግሞ ‹‹ሁዳዴ›› ይባላል፡፡ ኢትዮጵያዊው የዜማና የቅዱሳት መጻሕፍት ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚገኙትን ስምንት ሣምንታት ለትምህርት፣ ለአዘክሮና ለምስጋና በሚመች መልኩ ልዩ ስያሜዎች ሰጥቷቸዋል፡፡ ስለሆነም በእያንዳንዱ ሳምንት (ሰንበት) የሚነበቡ፣ የሚተረጎሙ፣ የሚዘከሩ፣ የሚዘመሩ ልዩ ልዩ መጽሐፍ ቅዱሣዊ ኩነቶችና አስተምህሮዎች አሉ፡፡

‹‹ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው›› (ማቴ.፬፥፩)

በወንጌል ቅዱስ ማቴዎስ ስለ ጌታችን መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስ ዐቢይ ጾም ሲጽፍ  ‹‹ከዚያ ወዲያ›› በማለት ከጀምረ በኋላ እርሱ ለሰዎች ድኅነት ሲል ለዐርባ ቀንና ሌሊት ያለ መብልና መጠጥ በጾም በምድረ በዳ እንደቆየ ይገልጽልናል፡፡

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን 

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የሚዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

ኪዳነ ምሕረት

የክርስቲያን ወገኖች ሁሉ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ፡፡ መታሰቢያዋን ለሚያደርግ፣ ስሟን ለሚጠራ፣ ለድኆችና ለችግረኞች እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ድረስ ለሚሰጥ የክብር ባለቤት ከሆነ ልጇ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ቃል ኪዳን ተቀብላለችና፡፡

ቃል ኪዳን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንጉሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…እናንት ልጆች የአባትን ተግሣጽ ስሙ፤ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ›› (መዝ.፬፥፩) በማለት እንደተናገረው የአባቶቻችሁን ተግሣጽ (ምክርና ቁጣ) ሰምታችሁ፣ በእግዚአብሔር ጥበቃ ከትላንት ዛሬ የደረሳችሁ ልጆች! ለዚህ ያደረሰንን እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ታሪክ ስለ እመቤታችን ቃል ኪዳን ነው፤ ቃል ኪዳን ማለት ‹‹ውል ወይም ስምምነት›› ማለት ነው፤ እግዚአብሔር ከአባቶቻችን ጋር በተለያየ ጊዜ ቃል ኪዳንን ገብቷል፤ እንደ ትእዛዙ ለሚኖሩ የሚፈልጉትን ሊያደርግላቸው ቃል ኪዳንን ሰጥቷቸዋል፤ በነቢዩ ሕዝቅኤል ‹‹የሰላምም ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር አደርጋለሁ፤ ዘለዓለም ቃል ኪዳን ይሆንላቸዋል፤ እኔም እባርካቸዋለሁ፤ አበዛቸውማለሁ፤ መቅደሴንም ለዘለዓለም በመካከላቸው አኖራለሁ…›› (ሕዝ.፴፯፥፳፮) በማለት ነግሮናል፡፡

የ ‹ሀ፣ አ፣ ወ እና የ› በግሥ ርባታ የሚያመጡት ለውጥ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን ስለ ዐበይት አናቅጽ እና ዐሥራው አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና የ ‹‹ሀ፣ አ፣ ወ እና የ›› የሚያመጡት የርባታ ለውጥ በግሥ ርባታ እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ግእዝ ዘኢትዮጵያ

እፎ ኃደርክሙ…

ተናገረው ይውጣ እንጂ አንደበትህ አይዘጋ
የአባቶችህ መገለጫ ዜማቸውን አትዘንጋ