ሐዊረ ሕይወት ማለት…

ይህ ሁለት ቃል ተናቦ ፫ ሱባዔ (፳፩) ትርጉምን ይሰጠናል።
፩.    ቃል በቃል የሕይወት ጉዞ ማለት ነው።
፪.    የሕይወት ኑሮ ማለት ይሆናል።
“ሕይወት እንተ አልባቲ ሞት = ሞት የሌለባት የሕይወት ፍሬ/ኑሮ።” ዕዝ. ሱቱ. ፭፥፲፫
ደግሞም “ይኄይስ መዊት እመራር ሕይወት = ከመራር ኑሮ ሞት ይሻላል።” ሢራ ፴፥፲፯
፫.    የመዳን ጉዞ፣ ወይም የደኅንነት ጉዞ፣
“ዛቲ ይእቲ ቀዳሚት ሕይወት = ይህች የመጀመሪያዋ ትንሣኤ ድኅነት ናት።” ራእ ፳፥፭
ደግሞም “መጻእኪ ለሕይወትኪ = ለሕይወትሽ፣ ለደኅንነትሽ መጣሽ።” ዮዲ. ፲፮፥፫
፬.    የፈውስ ጉዞ፣ ወይም የጤንነት ጉዞ፣
“ወሰሚዖሙ ሕይወተ እሙታን = ከሙታን ተለይቶ መነሣትንም በሰሙ ጊዜ” ግ.ሐዋ. ፲፯፥፴፪
፭.    የመኖር ጉዞ፣

፮.    የመሥራት ጉዞ፣
“ዘለዓለም ዘየሐውር በጽድቅ = ለዘለዓለም ሕግን የሚሠራ” ኢሳ. ፴፫፥፲፭
፯.    የዕድሜ ልክ ጉዞ
“እሴብሖ ለእግዚአብሔር በሕይወትየ = በሕይወቴ ዘመን ሁሉ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ።” መዝ ፻፵፭፥፪
፰.    የትንሣኤ ወይም የመታደስ ጉዞ፣
፱.    የጸሎተ ምሕላ ወይም የመማፀን የምጥንታ ጉዞ
፲.    የደስታ ጉዞ “ሐይወ ልቡ ወነፍሱ ለያዕቆብ = የያዕቆብ ልቡናው ሰውነቱ ደስ አላት ታደሰች።” ዘፍ ፵፭፥፳፮
፲፩.    የነፍስ ጉዳይ ጉዞ፣ ወይም የሰውነት ጥበቃ ጉዞ
፲፪.    መልአካዊ ጉዞ
፲፫.    ክርስቶሳዊ ጉዞ
፲፬.    የአካላዊ ሕይወት፣ የልብሰ ሕይወት፣ የእሳተ ሕይወት፣ የብርሃነ ሕይወት፣ የመንፈስ ቅዱስ ጉዞ፣
፲፭.    የክርስቲያን ጉዞ
፲፮.    የቀና ልብ ወይም የመልካም ሐሳብ ጉዞ
፲፯.    የነፍስ ዕውቀት ማለት የብልኅነት ጉዞ
፲፰.    የትዕግሥት፣ የጸጥታ ጉዞ
፲፱.    ትምህርታዊ ጉዞ
፳.     የመንፈሳዊ ፈቃድ ጉዞ
፳፩.    የምክር፣ የጉባኤ ጉዞ
፳፪.    የሥልጣናዊ ምርጫ የችሎታ ጉዞ ማለት ሁሉ ነው።

 

የዲላ ዮኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ የተመሠረተበትን አስራ ስድስተኛ ዓመቱን አከበረ

መጋቢት 6 ቀን 2005 ዓ.ም.


በዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ

በማኅበረ ቅዱሳን በዲላ ወረዳ ማእከል ሥር የሚገኘው የዲላ ዮኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ የተመሠረተበትን ዐሥራ ስድስተኛ ዓመቱን በዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በደመቀ ሁኔታ አከበረ፡፡

ግቢ ጉባኤው ከየካቲት 29 ቀን እስከ መጋቢት 1 ቀን 2005 ዓ.ም የተመሠረተበትን በዓል ሲያከብር በማኅበረ ቅዱሳን የአዋሣ ማእከል ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡ ማእከሉ በወከለው በአቶ ታደሰ ፈንታ በኩል ባስተላለፈው መልእክት “ዛሬ የምሥረታ በዓላችሁን የምታከብሩ ተማሪዎች ከመደበኛው ትምህርታችሁ ጎን ለጎን መንፈሳዊ ተግባራችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን በማቅረብ ነው” በማለት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

 

አያይዞውም “የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች በዕድሜ ዘመናችሁ ሁሉ በሥርዓተ አምልኮ መጽናት፣ በግቢ ቆይታችሁ በምታገኙት መንፈሳዊ ዕውቀት በመደገፍ ሀገራችሁንና ቤተ ክርስቲያናችሁን ማገልገል፣ ማኅበራችሁ ማኅበረ ቅዱሳን አሁን በመስጠት ላይ ያለውን አገልግሎት በማጠናከርና ከማኅበሩ ጎን በመሆን ለቤተ ክርስቲያን ያላችሁን ታማኝነት ትወጡ ዘንድ እናሳስባችኋለን” ብሏል፡፡

የዲላ ዮኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ጉባኤ ሰብሳቢ ተማሪ ገብሬ ወርቁ ስለግቢው ምሥረታ በዓል አከባበር ሲናገር “የዘንድሮን ምሥረታ በዓል ግቢ ጉባኤው ሲያከብር ወጣቶች ቤተ ክርስቲያን የምትጠብቅባቸውን መንፈሳዊ አገልግሎት በብቃት እንዲወጡ ለማስቻል በማሰብ ነው” ብሏል፡፡

 

የዲላ ዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መላከ ሰላም አምሳሉ ሣለ በምሥረታ በዓሉ ላይ በመገኘት አባታዊ ምክራቸውን የለገሱ ሲሆን መላከ ሰላም አምሳሉ በምክራቸው “የዲላ ዮኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ በዚህ ደብር መኖሩ በቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል አገልግሎት ላይ ከፍተኛ መንፈሳዊ አስተዋጽኦ አድርጓል፤ በመሆኑም የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የምሥረታ በዓላችሁን ስታከብሩ መንፈሳዊ አገልግሎታችሁን ወደ ፊትም አጠናክራችሁ ለመቀጠል በማሰብ መሆን አለበት” ሲሉ መክረዋል፡፡

በምስረታ በዓሉ ላይ በተጋባዥ መምህራንና መዘምራን፣ በተመራቂ ተማሪዎች እና በግቢ ጉባኤው ተማሪዎች ስብከቶች፣ መዝሙሮችና ልዮ ልዮ መንፈሳዊ መርሐ ግብራት ቀርበዋል፡፡ እንዲሁም ከሠላሳ በላይ የሚሆኑ የግቢው ተመራቂ ተማሪዎች በምስረታ በዓሉ ላይ በመገኘት ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ልምዳቸውንና ተሞክሯቸውን አካፍለዋል፡፡

አቶ ፍፁም ኩራባቸው የ2001 ዓ.ም የዲላ ዮኒቨርስቲ ተመረቂ ሲሆን በምሥረታ በዓሉ ላይ በመገኘቱ የፈጠረበትን ስሜት ሲናገር “በምሥረታ በዓሉ ላይ በመገኘት ሳከብር ቀድሞ በግቢ ውስጥ የነበረኝን መንፈሳዊ አገልግሎት በማስታወስ ወደ ፊት በበለጠ ለማገልገል የሚያስችለኝን መንፈሳዊ ስንቅ የምንሰንቅበትና ለግቢ ተማሪዎች ከወንድሞቻችን ጋር በመሆን ተሞክሯችንን የምናስተላልፍበት ልዮ ጊዜ በመሆኑ በጣም ደስተኛ ነኝ” ሲል ተናግሯል፡፡

በተያያዘም በምሥረታ በዓሉ ላይ የግቢ ጉባኤው የአዳራሽ አሠሪ ኮሚቴ ግቢ ጉባኤው በ600 ካሬ ሜትር ላይ እየሠራ ያለው አዳራሽ እየተፋጠነ እንደሆነ ገልጸል፡፡ የአዳራሽ አሠሪ ኮሚቴው በተወካያቸው በተማሪ ፍርዴ ጥላሁን በኩል ባቀረበው ሪፖርት “ተማሪዎች ቃለ እግዚአብሔር የሚማሩበትን አዳራሽን ለመሥራት እስከ አሁን አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ብር እንደፈጀና በቀጣይ ሊሠሩ ስላሰቧቸው የበር፣ የመስኮት፣ የኮርኒስ እንዲሁም የማጠቃለያ ሥራ የዕርዳታ ጥሪ” አቅርበዋል፡፡

የዲላ ዮኒቨርስቲ ግቢ ጉባኤ በተማሪዎች ከፍተኛ ትጋትና በአካባቢው ምእመናን ተነሳሽነት የዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያንን አንጾ ቅዳሴ ቤቱን በ1994 ዓ.ም እንዲከበር ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡ 

 

hawir hiwot

===== ዜና ሐዊረ ሕይወት ======

hawir hiwot
የሐዊረ ሕይወት ጉዞ አዘጋጅ ኮሚቴ ወደ ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በመሄድ የመንገዱንና የቦታውን ምቹነት አረጋግጦ መጣ፡፡
ዝግጅቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን የትኬት ሥርጭቱም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡


አጫጭር መረጃዎች

 

ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል፡-

 

ቦታው : ከአዲስ አበባ ወደ አምቦ መስመር ላይ 40(?) ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን የመንገዱ ጥራት ለማንኛውም ተጓዥ ምቹ መሆኑ ታይቷል፡፡

የእግር መንገድ? መኪና እስከ ቤተክርስቲያኑ የሚደርስ በመሆኑ የእግር መንገድ አይኖረውም፡፡ ይህም የዐቅም እና የጤና ችግር ላለባቸው ጥሩ ዜና ነው፡፡\

የመኪና ማቆሚያ? እስካሁን ከተደረጉት ጉዞዎች ከ100 በላይ መኪና ሊያስተናግድ የሚችል ሰፊና ውብ የሆነ ቦታ እንዳለው ተረጋግጧል፡፡


የተዘጋጁ ትኬቶች ስንት ናቸው? የተጓዥ ብዛትስ?

5000 ቲኬቶች ተዘጋጅተዋል(ካለፈው ዓመት በአንድ ሺህ ቁጥር ጭማሪ ይኖረዋል)፡፡በመሆኑም በዚህ ጉዞ ከአስተናጋጆች ጋር ከ5500 በላይ ተሣታፊዎች እነደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡

የትኬት ሥርጭት፡- የተዘጋጁት ትኬቶች ውስጥ 4800 በላይ ትኬቶች ከአዘጋጅ ኮሚቴው እጅ የተሰራጩ ሲሆን ሽያጩም ካለው ጊዜ አኳያ በሚያስገርም ሁኔታ በፍጥነት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡hawir hiwot 2005

ስንት አሰተናጋጆች ይኖራሉ? ይህን ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ከአበው ጸሎት ጋር ትኬት በመሸጥ ፣ በምግብ ዝግጅት፣ በመኪና ላይ መስተንግዶ፣ በመዝሙር ፣በሕክምና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ ኤሌክትሪክ፣ጽህፈት እና ሌሎችም ከ400 በላይ አገልጋዮች ይኖራሉ፡፡

ትኬቱ የት ይገኛል?
በማስታወቂያ በተገለጹበት ቦታዎችና እንዲሁም በየወረዳ ማእከላቱ ይገኛል፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ በማኅበሩ ሕንጻ ላይ የሚሸጠው ትኬት ይጠናቀቃል፡፡
ምን ዝግጅቶች አሉ?

ምግብ፡- ለተጓዦች የሚስማማ ምግብ እየተዘጋጀ ሲሆን በጥንቃቄ ለሁሉም ጤና በሚስማማ መልኩ የሚዘጋጅ ይሆናል፡፡
ድንኳን፡– ከ5000 – 6000 ሰው የሚይዝ ድንኳን ይዘጋጃል፡፡
ጀኔሬተር፡ መብራት ቢጠፋ ለመጠቀም የሚያስችል ጀኔሬተር ይኖራል፡፡
ሕክምና፡- በጉዞው ላይም ሆነ በቦታው ለሚፈጠሩ የጤና ችግር ልዩ የሕክምና ቡድን ከአስፈላጊ መድሃኒቶችና የሕክምና መሳሪያ ጋር ይኖራል፡፡
ቀጥታ ሥርጭት፡- ሥርጭቱ በመላው ዓለም ለሚገኙ ምዕመናን ከስፍራው በቀጥታ ለማስተላለፍ ዝግጅት ይደረጋል፡፡

ማሳሰቢያ፡- ከአ.አ ውጭ ያሉ ተጓዦች ከወዲሁ ትኬት ሣያልቅ እንዲመዘገቡ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡

ባለፈው ዓመት ከአ.አ ውጭ ከሰንዳፋ፣ ወሊሶ፣ አምቦ፣ ጅማ፣ ደ/ዘይት፣ ሞጆ፣ ባህር ዳር፣ መቀሌ፣ ደሴ፣ አፋር አዳማ(ናዝሬት)በርካታ ተጓዦች እነደነበሩ ይታወሳል፡፡

የአዘጋጅ ኮሚቴው ስጋት! በባለፉት ጉዞዎች እንደታየው ትኬቱ አስቀድሞ ስለሚያልቅ ትኬት ፈላጊ ምዕመናንን ማስተናገድ አለመቻል ነው፡፡

ማሳሰቢያ፡- በክርስቲያናዊ ሕይወትዎ እንዲመለስልዎት የሚፈልጉትን ማንኛውንም ጥያቄ በe-mail፡ hawirehiywot@yahoo.com አድራሻ ያቅርቡ፡፡ አባቶች በዕለቱ ከልምዳቸው በመነሳት መልስ ይሰጥዎታል፡፡ (hawirehiywot@yahoo.com)

ልብ ይበሉ! መረጃዎችን መከታተል ትኬቱን ይዞ ነው!

የድምጽ ማስታወቂያውን ለማድመጥ እዚህ ይጫኑ!

++++++ በጸሎትዎ ያስቡን! ++++++



abune mathias1

ቅዱስነታቸው የመጀመሪያ እንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላለፉ

የካቲት 28 ቀን 2005ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

abune mathias1ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የአብይ ጾምን በማስመልከት የካቲት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡

 

ቅዱስነታቸው ባስተላለፉት መልእክት “ለእግዚአብሔር ሕግ መገዛት እስከተቻለ ድረስ ክፉውንና በጎውን ለይቶ ማወቅ ስለማያዳግት በተቻለ መጠን ከፊታችን ሰኞ መጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. በሚጀመረው በታላቁ ጾማችን በዓብይ ጾም ወራት ጎጂ ከሆኑ ተግባራት ሁሉ መራቅ አለብን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን የማዳን ሥራ ከመጀመሩ በፊት ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊት በመጾም ድኅነተ ነፍስ እንዳስገኘልን ሁሉ እኛም ፈለጉን ተከትለን ጾም በመጾም ጥንካሬን አግኝተን ረቂቅ የሆነውን የዲያብሎስ ፈተና ማሸነፍ በሚያስችለን ቀጥተኛ መንገድ ለመጓዝ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅብናል” ብለዋል፡፡

የጾም ዋና ዓላማው ለእግዚአብሔር ቃል በሙሉ ኃይል ለመታዘዝ መዘጋጀት እንደሆነ የገለጹት ቅዱስ ፓትርያርኩ በጾም ወራት ሊፈጸሙ ይገባቸዋል ያሏቸውንም ሲጠቅሱ “ተግባራችን ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ሊሆን የሚችለው ርኅራኄን፤ ቸርነትን፤ ምጽዋትን፤ ፍቅርን፤ ስምምነትን፤ ትሕትናን፤ መረዳዳትን፤ መተዛዘንን ገንዘብ አድርገን የጾምን እንደሆነ ነው፡፡ በጾም ወራት ልንፈጽማቸው የሚገቡን የትሩፋት ሥራዎች ብዙዎች ቢሆኑም በተለይ መሠረታዊ የሆነ የኑሮ ፍላጎት ላልተሟላላቸው ወገኖቻችን ማለትም ልብስ ለሌላቸው ልብስ በማልበስ፤ የምግብ እጥረት ላጋጠማቸው የሚቻለንን በመለገስ፤ ማረፊያ ለሌላቸው መጠለያዎችን በመቀለስ ወገኖቻችንን መርዳት ያስፈልጋል” በማለት መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር ዘፍ.35፥1

የካቲት 27 ቀን 2005 ዓ.ም.

ዲ/ን ሰለሞን መኩሪ

ይህንን የተናገረ አምላካችን እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ የተነገረው እስራኤል ለተባለ ያዕቆብ ነው፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ ታሪኩ ተጽፎ እንደምናገኘው ከወንድሙ ከዔሳው ሸሽቶ የአባቱን የይስሐቅን በረከት ተቀብሎ ወደ አጎቱ ወደ ላባ ሲሄድ ሎዛ ከምትባለው ምድር ሲደርስ ጊዜው መሸ፡፡ እርሱም ደክሞት ስለነበር ድንጋይ ተንተርሶ ተኝቶ ሳለ ሌሊት በራእይ እግዚአብሔር ተገለጠለት ራእዩም የወርቅ መሰላል ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ በመሰላሉ መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም በዙፋኑ ተቀምጦ ነበር፡፡

 

ያዕቆብንም “እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ፤ አትፍራ፣ ይህችን አንተ የተኛህባትን ምድር ለአንተም ለዘርህም እሰጣለሁ ዘርህም እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናል፡፡ በአንተ በዘርህ አሕዛብ ይባረካሉ፡፡ እነሆም እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፡፡ የነገርኩህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህም” አለው፡፡ ያዕቆብም ከእንቅልፍ ተነሥቶ በእውነት እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ አለ፤ እኔ አላወቅሁም ነበር፡፡

 

ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራል? ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህችም የሰማይ ደጅ ናት፡፡ ያዕቆብም ማልዶ ተነሣ ተንተርሷት የነበረችውንም ድንጋይ ወስዶ ሐውልት አድርጎ አቆማት፤ በላይዋም ዘይት አፈሰሰባት፡፡ ያዕቆብም ያን ሥፍራ ቤቴል ብሎ ጠራው አስቀድሞ ግን የዚያ ከተማ ስም ሎዛ ነበር፡፡ ያዕቆብም ስዕለትን ተሳለ፡፡ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ቢሆን በምሄድበት መንገድ ቢጠብቀኝ፣ የምበላውን እንጀራ የምለብሰውን ልብስ ቢሰጠኝ ወደ አባቴ አገር በሰላም ቢመልሰኝ እግዚአብሔር አምላኬ ይሆንልኛል፡፡ ለሐውልት ያቆምኳት ይህች ድንጋይ የእግዚአብሔር ቤት ትሆንልኛለች፤ ከሰጠኸኝ ሁሉ ለአንተ ከአስር እጅ አንዱን እሰጥሃለሁ አለ፡፡ እግዚአብሔርም ስእለቱን ሰምቶ ሁሉንም ፈጸመለት ወደ አጎቱ ወደ ላባ ደርሶ ሚስት አግብቶ ብዙ ልጆችን ወልዶ እንዲሁም ብዙ ባሮችን እና ሀብት ንብረት አፍርቶ ወደ አባቱ ሀገር ሲመለስ እግዚአብሔር አምላክ ተገለጠለትና “ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር” ብሎ አዘዘው ዘፍ.28፥10-20፣ ዘፍ.35፥1፡፡

x

 

ለመሆኑ ይህች ቤቴል ማን ናት? እግዚአብሔር አምላክ ለጊዜው ያዕቆብና ቤተሰቡ እንዲኖሩባት ለፍጻሜው ሁላችንም እንድንኖርባት የታዘዝንባት ቤቴል ምስጢራዊ ትርጉሟ ምን ይመስላል? አባቶቻችን እንዲህ ይተረጉሙታል፡፡

 

1.    ቤቴል የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡

አባታችን ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ባየው ራእይ እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ገልጾለታል፡፡ ይኸውም የወርቅ መሰላል ከምድር እስከ ሰማይ ድረስ ተተክሎ በመሰላሉ መላእክት ከላይ ወደ ታች ሲወርዱ እና ሲወጡ ተመልክቷል፡፡ በመሰላል የላዩ ወደ ታች እንዲወርድ አምላክ ሰው ለመሆኑ የታቹ ወደ ላይ እንዲወጣ ሰው አምላክ ለመሆኑ ምክንያት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ መሰላሉ ደግሞ ወርቅ ነበር፡፡

 

ወርቅ ፅሩይ ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በማሰብ፣ በመናገር፣ በመተግበር፣ በመዳሰስ፣ በማሽተት ወ.ዘ.ተ. ሰው ሁሉ ኀጢአት በሚሠራበት ህዋስ ሁሉ ያልተዳደፈች፣ ንጽሕት፣ መልዕልተ ፍጡራን /ከፍጡራን በላይ/ መትሕተ ፈጣሪ /ከፈጣሪ በታች/ ናት፡፡ ከነገደ መላእክት ከደቂቀ አዳም በክብር የሚመስላት በጸጋ የሚተካከላት የለም፡፡ ይህንንም ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ ሲገልጽ “የዐቢ ክብራ ለማርያም እምኩሎሙ ቅዱሳን” “የማርያም ክብር ከቅዱሳን ክብር ይበልጣል” ብሏል፡፡

 

በወርቁ መሰላል መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ መታየታቸው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምዕራገ ጸሎት እንደሆነች በእመቤታችን ምልጃ የሰው ሁሉ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር እንደሚቀርብ የእግዚአብሔርም ቸርነት ለሰዎች እንደሚሰጥ ያመለክታል፡፡ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ “አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌኪ ማርያም ዘየዓርግ ሎዓሌ” ብሎ አጉልቶታል በወርቁ መሰላል ጫፍ ዙፋን ነበር፡፡ በዙፋኑም ላይ እግዚአብሔር ተቀምጦ ለያዕቆብ ተገልጦለታል፡፡ ባርኮታል፤ ዙፋን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል የማኅፀኗ ምሳሌ ነው፡፡ በማኅፀኗም ፍጥረቱን ለማዳን እግዚአብሔር ሰው እንደሆነ ማለትም በማኅፀነ ድንግል መፀነሱን ያመለክታል፡፡ ከዚያም በአጭር ቁመት በጠባብ ደርት በሰው መጠን መገለጹን ያስረዳል፡፡ ያዕቆብን እንደባረከው ርስት እንደሰጠው ሁሉ በእመቤታችን ሥጋ ተገልጦ በበደሉ ምክንያት የተረገመውን ሰው እንደባረከው አጥቶት የነበረውን ርስት ገነት መንግሥተ ሰማያትን እንደሰጠው ያመለክታል ዮሐ.14፥2፡፡ “በአባቴ ቤት ብዙ ማደሪያ አለ ቦታ  አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፡፡ ዳግመኛም እመጣለሁ እናንተም እኔ ባለሁበት ትኖሩ ዘንድ ወደ እኔ እወስዳችኋለሁ” እንዲል፡፡ ፍጥረቱም ሁሉ ፈጣሪው እግዚአብሔር ተመለከተው፡፡

 

ፍጥረት ማለትም መላእክትና ደቂቀ አዳም ፈጣሪያቸው እግዚአብሔርን ለመመልከት የቻሉት በእመቤታችን ሥጋ በመገለጡ ነው፡፡ ያዕቆብ ተንተርሶት የነበረው ድንጋይ እመቤታችን በትንቢተ ነቢያት ጸንታ መኖሯን ያመለክታል፡፡ እንግዲህ ይህችን ነቢያት በትንቢታቸው ደጅ ሲጠኗት የነበረችውን እግዚአብሔር የተገለጠባት የእግዚአብሔር ዙፋን ጸሎትን መሥዋዕትን ሁሉ የምታሳርግ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን አማላጅ መጠጊያ ልናደርግ ያስፈልጋል፡፡ ያዕቆብ በቤቴል እንዳደረ እኛም በአማላጅነቷ ከልጇ ዘንድ በተሰጣት የከበረ ቃል ኪዳን ልባችንን እንድናኖር ያስፈልጋል መዝ.47፥12፡፡ “በብርታቷ ላይ ልባችሁን አኑሩ” እንዲል፡፡ የእመቤታችን ምልጃ ለሁላችንም ይደረግልን፡፡

 

2.    ቤቴል የተባለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡

አባታችን ያዕቆብ ባየው ራእይ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ክብር እግዚአብሔር ገልጦለታል፡፡ ያዕቆብ የጳጳሳት የቀሳውስት ምሳሌ ነው፡፡ ቦታው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ የተንተራሰውን ድንጋይ ዘይት አፍስሶበታል፡፡ ለጊዜው ቦታው እንዳይጠፋበት ለምልክት ለፍጻሜው ሊቃነ ጳጳሳት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በቅብዐ ሜሮን እንደሚያከብሯት የመንፈስ ቅዱስ የጸጋው ግምጃ ቤት እንደሚያደርጓት ማሳየቱ ነው፡፡ ሐዋ.20፥28፡፡ የወርቁ መሰላል ምሳሌዋ የሆነ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዘለዓለማዊ ድንግልና ክብር አማላጅነት የሚነገርባት እግዚአብሔር የታየባት ዙፋኑ የተዘረጋባት ይኸውም የታቦቱ ምሳሌ ነው፡፡ መላእክት የእግዚአብሔርን ቸርነት ወደ ሰው ልጆች የሚያመጡባት የሰው ልጆችን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የሚያሳርጉባት ዘወትርም በኪዳን በቅዳሴ በማኅሌት በሰዓታት የማይለያት የምሕረት አደባባይ አማናዊት ቤቴል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡

 

አምላካችን እግዚአብሔር ለቅዱስ ያዕቆብ “ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር” ሲል አዞታል፡፡ ምክንያቱም ሕይወት የሚገኝባት በሥጋ በነፍስ የምንጠበቅባት ስለሆነ ነው፡፡ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት በደብረ ታቦር የጌታችንን ብርሃነ መለኮቱን በተመለከቱ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ “በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው” ማቴ.17፥4 እንዳለ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን መኖር ለእኛ መልካም ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊትም እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንኩት እርሷንም እሻለሁ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ …. ቤተ መቅደሱንም አገለግል ዘንድ እንዳለ መዝ.26፥4፡፡ ቅዱስ ዳዊት መንግሥቱ እንዲደላደልለት ዙፋኑ እንዲጸናለት ያይደለ በእግዚአብሔር ቤት መኖር እንዲገባ አጥብቆ እግዚአብሔርን የለመነበት ልመና ነው፡፡ ይህም የተወደደ ሆኖለታል፡፡ እንግዲህ በእግዚአብሔር ቤት በአማናዊት ቤቴል ለመኖር እንዴት ሆነው ተዘጋጅተው መውጣት /መሄድ/ እንደሚገባቸው ያዕቆብ ለቤተሰቡ አስገነዘባቸው እንዲህ አላቸው፡፡

 

1.    እንግዶች አማልክትን ከእናንተ አስወግዱ አላቸው፡፡

አባታችን ያዕቆብ ለቤተሰቦቹና ከእርሱ ጋር ላሉት “ከእናንተ ጋር ያሉ እንግዶችን አማልክት ከእናንተ አስወገዱ” አላቸው አምላካችን እግዚአብሔር በአምልኮቱ የሚገባበትን አይወድም በሊቀ ነቢያት በሙሴ አድሮ ሲናገር “ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክትን አታምልክ” ዘጸ.20፥3 ብሏል፡፡ ሰማይና ምድርን በውስጧ ያሉትን የሚታየውንና የማይታየውን ፈጥሮ በመግቦቱ በጠብቆቱ የሚያስተዳድር እግዚአብሔር ሆኖ ሳለ ከእግዚአብሔር ሌላ አምላክ አጥንት ጠርቦ ድንጋይ አለዝቦ፣ በጨሌ፣ በዛፍ፣ በተራራ፣ በጠንቋይ ወ.ዘ.ተ. ማምለክ አይገባም፡፡ እንዲህ በሚያደርጉ ሰዎች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣው ትነዳለችና ዘጸ.20፥4፡፡ ዛሬም በዘመናችን ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣዖት ሆነው ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጡ ሰዎች አሉ፡፡ ጠዋት ቤተ ክርስቲያን መጥተው ኪዳን አድርሰው ቅዳሴ አስቀድሰው ለእግዚአብሔር የሚገባውን እጣኑን ጧፉን ዘቢቡን ሌላም ለቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልገውን ሰጥተው ሰግደው አምልኮታቸውን ፈጽመው ደግሞ ሲመሽ ሰው አየኝ አላየኝ ብለው ጨለማን ተገን አድርገው ጫት፣ ሰንደል፣ ቡና፣ ቄጤማ ተሸክመው ወደ ቤተ ክርስቲያን በሄዱበት እግራቸው ወደ ጠንቋይ ቤት የሚሄዱ በዚያ የሚሰግዱ በቤታቸውም ጠንቋዩ ያዘዛቸውን ጨሌ የሚያስቀምጡ ቀን እና ወር ለይተው ጥቁር በግ ገብስማ ዶሮ ወ.ዘ.ተ.

 

የሚያርዱ እህል የሚበትኑ እንደዚህ ባለ በሁለት እግር በሚያነክስ ልብ ወይም ሁለት እግር አለኝ ብሎ ሁለት ዛፍ ላይ ሊወጣ የሚመኝ ሰው ከእግዚአብሔር አንዳች ነገር አያገኝም፡፡ ስለዚህ ይህንን ሰይጣናዊ ልምድ አስወግዶ ማለትም ከዚህ የኀጢአት ሥራ ንስሐ ገብቶ ተለይቶ በፍጹም ልብ በፍጹም ነፍስ እግዚአበሔርን ብቻ በማምለክ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መገስገስ ያስፈልጋል፡፡ የያዕቆብ ቤተሰቦች የአባታቸውን ምክር ሰምተው የጣዖት ምስል ተቀርፆባቸው የነበሩ በእግራቸውና በእጃቸው በጆሮአቸውም የነበሩትን አውልቀው ለያዕቆብ ሰጡት እርሱም እንዳያገኟቸው አድርጎ አርቆ ቀበራቸው፡፡ እስከ ዛሬም አጠፋቸው ዘፍ.35፥4 እንዲል፡፡ ያዕቆብ የቀሳውስት ምሳሌ ነው፡፡ ቤተሰቦቹ የምእመናን ምስሎቹን አምጥቶ ለያዕቆብ እንደመስጠት ኀጢአትን ለካህን መናዘዝ ከአምልኮ ጣዖት እንደመለየት ሲሆን ያዕቆብ ወስዶ እንደ ቀበራቸው በቀኖና ወደ እግዚአብሔር የመቅረብ ምሳሌ ነው፡፡ ከአምልኮ ጣዖት ተለይተን እግዚአብሔርን ብቻ እያመለክን በቤቱ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንድንኖር የቅዱሳን አምላክ ይርዳን፡፡

 

2.    ንጹሐን ሁኑ ልብሳችሁን እጠቡ አላቸው፡፡

አባታችን ያዕቆብ ለቤተሰቡ እንግዶችን አማልክትን እንዲያስወግዱ ካዘዙ በኋላ እነርሱም ካስወገዱ በኋላ የሰጣቸው መመሪያ “ንጹሐን ሁኑ ልብሳችሁን እጠቡ” አላቸው፡፡ ሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ አፍአዊ /የውጭ/ ንጽሕናውን እንዲሁም ውስጣዊ /የልብ/ ንጽሕናውን መጠበቅ እንደሚገባው አስተማረ ዘሌ.11፥44 እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ንጹሐንም ሁኑ እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር ቅዱስ ነኝና፡፡” ይላል ስለዚህ ወደ ቅዱስ እግዚአብሔር ወደ ክብሩ ዙፋን ወደ ጸጋው ግምጃ ቤት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ለመገናኘት ንጹሕ ልብስ ለብሰን ደግሞ በንስሐ ታጥበን ሕይወታችንን አድሰን ሊሆን ይገባል፡፡ ቅዱስ ዳዊትም በመዝ.50፥7 “በሂሶጵ እርጨኝ እነጻማለሁ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ፡፡” እንዲል፡፡

 

አንዳንድ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመሄድ የልብስ ንጽሕና መጠበቅ የሚገባ የማይመስላቸው ወደ አንድ ሰርግ ወይም ድግስ በሰው ፊት ለመታየት የሚያደርጉትን ጥንቃቄ እና የአለባበስ ሥርዓት ወደ ቤተ ክርስቲያን ግን ሲመጡ አልባሌ ሆነው መምጣት የሚገባ የሚመስላቸው አሉ አንዳንዶችም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ ሰውነትን የሚያራቁት /የሚያስገመግም/ ልብስ ለብሰው የሚመጡ አሉ ይህ የሚገባ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ለጸሎት የመጣውን ሰው አእምሮ የሚሰርቅና የሚያሰናክል እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ምስጢሩ ግን አባታችን ያዕቆብ ለቤተሰቡ ንጹህ ሁኑ ልብሳችሁን እጠቡ ማለቱ በንስሐ ሕይወት ተዘጋጅታችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በእግረ ልቡና ውጡ ለማለት ነው፡፡ ለዚህም የቅድስት ሥላሴ ቸርነት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላእክት ፈጣን ተራዳኢነት የቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ አይለየን ይርዳን አሜን፡፡

1-bealesimet

የ6ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሥርዓተ ሢመት ፈጸሙ

የካቲት 27 ቀን 2005ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

ሪፖርታዥ

1-bealesimet“የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አከብራለሁ አስከብራለሁ” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛ ፓትርያርክ ሆነው የተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሥርዓተ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደተፈጸመላቸው ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናንን ለማገልገል ቃለ መሐላ የፈጸሙ ሲሆን ከሰሜን አሜሪካ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚካሄደው የእርቀ ሰላም ሂደት እንደሚቀጥልም ተናግረዋል፡፡

 

በሥርዓተ ሢመቱ ላይ የመንግሥት ባለስልጣናት፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የአኀት ቤተ ክርስቲያናት ልዑካን ምእመናን በተገኙበት በፈጸሙት ቃለ መሐላ “. . . የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት፤ የሁሉም አባት ሆኜ በእኩልነት፤ በግልጽነትና በታማኝነት በፍቅርና በትሕትና አገለግላለሁ፡፡ በምሥጢረ ሥላሴና በምስጢረ ሥጋዌ ትምህርትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት አምኜ አስተምራለሁ፡፡ . . . የእግዚአብሔር ቸርነት፤ የድንግል ማርያም አማላጅነት፤ የቅዱሳን መላእክት፤ የቅዱሳን ነብያት፤ የቅዱሳን ሐዋርያት፤ የቅዱሳን ጻድቃን ሰማእታት ተራዳኢነትን በማመን ሁሉንም ለመባረክ፤ ለመቀደስና ለማገልገል ቃል እገባለሁ፡፡ በኒቅያ በ325 ዓ.ም. በ318ቱ ሊቃውንት፤ በቁስጥንጥንያ በ381 ዓ.ም. በ150 ሊቃውንት፤ በኤፌሶን በ431ዓ.ም. በ200 ሊቃውንት የተወሰነውን ትምህርተ ሃይማኖት፤ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አከብራለሁ፤ አስከብራሉ፡፡ ለዚህም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ቃል እገባለሁ” ብለዋል፡፡

 

በዐውደ ምሕረት ላይ በተካሄደው መርሐ ግብር የደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በዓሉን በማስመልከት2-bealesimet ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም  በጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተባበሪነት ከየቤተ ክርስቲያኑ የተውጣጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የቆሜ አጫበር ወረብ፤ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የመዝሙር ክፍል አባላት ለበዓሉ ያዘጋጁትን ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡

 

በመርሐ ግብሩ ላይ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃማኖት መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የኢሉባቦር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጰስ ባስተላለፉት መልእክት “ታሪካዊት፤ ጥንታዊት፤ ብሔራዊትና አለማቀፋዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በየጊዜው ከውስጥም ከውጪም የሚደርስባትን መከራና ፈተና ሁሉ በጸሎቷ፤ በትዕግስቷ ተቋቁማ በደሙ በዋጃትትና በመሠረታት በሚጠብቃትም በዓለም ቤዛ በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኀይል አሁን ካለችበት ደረጃ ደርሳለች፡፡ ጥንታዊትና የሁሉም በኩር የሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን ኋላ ቀር እንዳትሆንና ቀዳሚነቷንም እንደያዘች ትጓዝ ዘንድ ብዙ መሥራትና ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋትና ማጠናከር ይጠበቅባታል” ብለዋል፡፡ በተጨማሪም አምስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የጀመሯቸውን የልማት ሥራዎችና  ከዓለም አቀፍ አብያተ ክርስቲያናት ጋር ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያላትን ግንኙነት አጠናክራ እንድትቀጥል 6ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

 

በበዓለ ሲመቱ ላይ ከተገኙት የአኀት ቤተ ክርስቲያናት ልዑካን መካከል ከሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ባርቶማ ጳውሎስ 2ኛ ዘመንበረ ቶማስ የማንካራ ሜትሮ ፖሊታን ባስተላለፉት መልእክትም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛው ፓትርያርክ በዓለ ሢመት ላይ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ በሁለቱ አኀት ቤተ ክርስቲያናት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

 

3-bealesimetየግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በመወከል በበዓለ ሢመቱ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጳኩሚስ “በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ላይ በጣም ብዙ ችግሮችና ፈተናዎች ይታያሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የሚያጋጥሙን ፈተናዎችን ለመቋቋም እኛ የኦርየንታል ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናት የጌታችን የአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ለመፈጸም በአንድነት ሆነን መጸለይና መሥራት ይጠበቅብናል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የአሌክሳንድርያ ቤተ ክርስቲያን ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ያለንን የጠበቀ ግንኙነት አጠናክረን መቀጠል ይገባናል” ብለዋል፡፡

 

በበዓለ ሢመቱ ላይ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት የክቡር አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ መልእክት የቀረበ ሲሆን ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት መካከል ክቡር አቶ አባ ዱላ ገመዳ የኢፌዲሪ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ንግግር አድርገዋል፡፡ ባስተላለፉት መልእክትም “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ብቻ ሳትሆን የአገራችን ታሪክ አካል ናት” ብለዋል፡፡ በዚሁ በዓለ ሢመት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ተወካዮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን የአርመንና የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናት፤ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ተወካዮች መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

 

ከአኀት ቤተ ክርስቲያናት የተዘጋጁ ስጦታዎችን ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃማኖት የተሰጡ ሲሆን የፖርቱጋል አምባሳደር በ1622 እ. ኤ. አ. በፖርቱጋል ቋንቋ ተጽፎ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመውን “የኢትዮጵያ ታሪክ” የተሰኘውን ባለ ሁለት ቅጽ መጽሐፍ በስጦታ አበርክተዋል፡፡

 

በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ማትያስ በሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ “ በእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ4-bealesimet ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ባለው መንፈሳዊ ሥልጣን ምርጫው እንዲፈጸም ባሳለፈው ውሳኔ የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ተጨምሮበት ምርጫው ተከናውኗል፡፡ እግዚአብሔር ሥራውን የሚሠራው በሰው ላይ አድሮ ነው፡፡ ሓላፊነቱና ሸክሙ ከባድ ቢሆንም እንደ ፈቃድህ ይሁን በማለት የእግዚአብሔርን ጥሪ በትሕትና ተቀብዬዋለሁ፡፡ መታዘዝ ከመሥዋዕት ይበልጣልና፡፡ አቅሜ የፈቀደውን ያህል ለቤተ ክርስቲያኔ እታዘዛለሁ፡፡ አልችልም ማለት እችል ነበር ነገር ግን የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ አልቀበልም ማለት መሥዋዕትነትን መሸሽ ሆነ፡፡ ይህ መንፈሳዊ ሥልጣን የክርስቶስ መከራ መስቀልን ተሸክሞ ለመሥዋዕትነት መሰለፍ እንጂ ለክብርና ለልዕልና እንዳልሆነ ይገባኛል፡፡ ሁላችሁም እንደምትረዱኝም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እግዚአብሔር ይርዳኝ፡፡ ጸሎታችሁና ትብብራችሁ አይለየኝ፡፡ ይህንን ታላቅ ሓላፊነት  ከእግዚአብሔር እርዳታ ጋር ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጭምር እንጂ የእኔ ብቻ ሊሆን ስለማይችል በጋራ እንወጣዋለን የሚል ጽኑ እምነት አለኝ” ብለዋል፡፡

 

በተጨማሪም በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚደረገውን የእርቀ ሰላም ሂደት በማስመልከት “ለረጅም ጊዜ ሲያወዛግብ የከረመው የእርቅና የሰላም ጉዳይ ለጊዜው ባይሳካም በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ጥረቱ ይቀጥላል፡፡ ተስፋ አንቆርጥም” ብለዋል፡፡

 

በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በሐምሌ 2002 ዓ.ም. በየካቲት 2004 ዓ.ም. እንዲሁም በኅዳር 2005 ዓ.ም. ለሦስት ጊዜያት  እርቀ ሰላም ለማካሔድ ጥረቶች መደረጋቸው ይታወሳል፡፡

1-bealesimet

የ6ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሥርዓተ ሢመት ፈጸሙ

የካቲት 26 ቀን 2005ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ
ሪፖርታዥ
1-bealesimet

“የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አከብራለሁ አስከብራለሁ” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛ ፓትርያርክ ሆነው የተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሥርዓተ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደተፈጸመላቸው   ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናንን ለማገልገል ቃለ መሐላ የፈጸሙ ሲሆን ከሰሜን አሜሪካ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚካሔደው የእርቀ ሰላም ሂደት እንደሚቀጥልም ተናግረዋል፡፡
በሥርዓተ ሢመቱ ላይ የመንግስት ባለስልጣናት፤ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የአኀት ቤተ ክርስቲያናት ልዑካን ምእመናን በተገኙበት በፈጸሙት ቃለ መሐላ “. . . የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት ፤ የሁሉም አባት ሆኜ በእኩልነት፤ በግልጽነትና በታማኝነት በፍቅርና በትሕትና አገለግላለሁ፡፡ በምሥጢረ ሥላሴና በምስጢረ ሥጋዌ ትምህርትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት አምኜ አስተምራለሁ፡፡ . . . የእግዚአብሔር ቸርነት፤ የድንግል ማርያም አማላጅነት ፤ የቅዱሳን መላእክት ፤ የቅዱሳን ነብያት፤ የቅዱሳን ሐዋርያት ፤ የቅዱሳን ጻድቃን ሰማእታት ተራዳኢነትን በማመን ሁሉንም ለመባረክ፤ ለመቀደስና ለማገልገል ቃል እገባለሁ፡፡ በኒቅያ በ325 ዓ.ም. በ318ቱ ሊቃውንት ፤ በቁስጥንጥንያ በ381 ዓ.ም. በ150 ሊቃውንት ፤ በኤፌሶን በ431ዓ.ም. በ200 ሊቃውንት የተወሰነውን ትምህርተ ሃይማኖት ፤ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አከብራለሁ፤ አስከብራሉ፡፡ ለዚህም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ቃል እገባለሁ” ብለዋል፡፡
በአውደ ምሕረት ላይ በተካሔደው መርሐ ግብር የደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በዓሉን በማስመልከት ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም  በጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተባበሪነት ከየቤተ ክርስቲያኑ የተውጣጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የቆሜ አጫበር ወረብ፤ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የመዝሙር ክፍል አባላት ለበዓሉ ያዘጋጁትን ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃማኖት መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የኢሉባቦር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጰስ ባስተላለፉት መልእክት “ታሪካዊት፤ ጥንታዊት፤ ብሔራዊትና አለማቀፋዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በየጊዜው ከውስጥም ከውጪም የሚደርስባትን መከራና ፈተና ሁሉ በጸሎቷ፤ በትዕግስቷ ተቋቁማ በደሙ በዋጃትትና በመሠረታት በሚጠብቃትም በዓለም ቤዛ በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል አሁን ካለችበት ደረጃ ደርሳለች፡፡ ጥንታዊትና የሁሉም በኩር የሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን ኋላ ቀር እንዳትሆንና ቀዳሚነቷንም እንደያዘች ትጓዝ ዘንድ ብዙ መሥራትና ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋትና ማጠናከር ይጠበቅባታል” ብለዋል፡፡ በተጨማሪም አምስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የጀመሯቸውን የልማት ስራዎችና  ከዓለም አቀፍ አብያተ ክርስቲያናት ጋር ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያላትን ግንኙነት አጠናክራ እንድትቀጥል 6ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በበዓለ ሲመቱ ላይ ከተገኙት የአኀት ቤተ ክርስቲያናት ልዑካን መካከል ከሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ባርቶማ ጳውሎስ 2ኛ ዘመንበረ ቶማስ የማንካራ ሜትሮ ፖሊታን ባስተላለፉት መልእክትም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛው ፓትርያርክ በዓለ ሢመት ላይ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ በሁለቱ አኀት ቤተ ክርስቲያናት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በመወከል በበዓለ ሢመቱ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጳኩሚስ “በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ላይ በጣም ብዙ ችግሮችና ፈተናዎች ይታያሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የሚያጋጥሙን ፈተናዎችን ለመቋቋም እኛ የኦርየንታል ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናት የጌታችን የአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ለመፈጸም በአንድነት ሆነን መጸለይና መሥራት ይጠበቅብናል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የአሌክሳንድርያ ቤተ ክርስቲያን ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ያለንን የጠበቀ ግንኙነት አጠናክረን መቀጠል ይገባናል” ብለዋል፡፡
በበዓለ ሢመቱ ላይ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት የክቡር አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ መልእክት የቀረበ ሲሆን ከከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት መካከል ክቡር አቶ አባ ዱላ ገመዳ የኢፌዲሪ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ንግግር አድርገዋል፡፡ ባስተላለፉት መልእክትም “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ብቻ ሳትሆን የአገራችን ታሪክ አካል ናት” ብለዋል፡፡ በዚሁ በዓለ ሢመት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ተወካዮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን የአርመንና የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናት፤ የአለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ተወካዮች መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ከአኀት ቤተ ክርስቲያናት የተዘጋጁ ስጦታዎችን ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃማኖት የተሰጡ ሲሆን የፖርቱጋል አምባሳደር በ1622 እ. ኤ. አ. በፖርቱጋል ቋንቋ ተጽፎ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመውን “የኢትዮጵያ ታሪክ” የተሰኘውን ባለ ሁለት ቅጽ መጽሐፍ በስጦታ አበርክተዋል፡፡
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ማትያስ በሰጡት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ “ በእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ባለው መንፈሳዊ ሥልጣን ምርጫው እንዲፈጸም ባሳለፈው ውሳኔ የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ተጨምሮበት ምርጫው ተከናውኗል፡፡ እግዚአብሔር ሥራውን የሚሠራው በሰው ላይ አድሮ ነው፡፡ ሃላፊነቱና ሸክሙ ከባድ ቢሆንም እንደ ፈቃድህ ይሁን በማለት የእግዚአብሔርን ጥሪ በትህትና ተቀብዬዋለሁ፡፡ መታዘዝ ከመስዋእት ይበልጣልና፡፡ አቅሜ የፈቀደውን ያህል ለቤተ ክርስቲያኔ እታዘዛለሁ፡፡ አልችልም ማለት እችል ነበር ነገር ግን የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ አልቀበልም ማለት መሥዋእትነትን መሸሽ ሆነ፡፡ ይህ መንፈሳዊ ስልጣን የክርስቶስ መከራ መስቀልን ተሸክሞ ለመሥዋእትነት መሰለፍ እንጂ ለክብርና ለልዕልና እንዳልሆነ ይገባኛል፡፡ ሁላችሁም እንደምትረዱኝም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እግዚአብሔር ይርዳኝ፡፡ ጸሎታችሁና ትብብራችሁ አይለየኝ፡፡ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት  ከእግዚአብሔር እርዳታ ጋር ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጭምር እንጂ የእኔ ብቻ ሊሆን ስለማይችል በጋራ እንወጣዋለን የሚል ጽኑ እምነት አለኝ” ብለዋል፡፡
በተጨማሪም በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚደረገውን የእርቀ ሰላም ሂደት በማስመልከት “ለረጅም ጊዜ ሲያወዛግብ የከረመው የእርቅና የሰላም ጉዳይ ለጊዜው ባይሳካም በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ጥረቱ ይቀጥላል፡፡ ተስፋ አንቆርጥም” ብለዋል፡፡
በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በሐምሌ 2002 ዓ.ም. በየካቲት 2004 ዓ.ም. እንዲሁም በኅዳር 2005 ዓ.ም. ለሦስት ጊዜያት  እርቀ ሰላም ለማካሔድ ጥረቶች መደረጋቸው ይታወሳል፡፡
abune mathias entronment

የ6ኛው ፓትርያርክ ሥርዓተ ሢመት ተፈጸመ

የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛ ፓትርያርክ ሆነው የተመረጡት የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሥርዓተ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተፈጸመ፡፡

ከዋዜማው ጀምሮ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የማኅሌት ጸሎት በማድረስ የተጀመረው ሥርዓተ ጸሎት ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከአቃቤ መንበረ ፓትርያርኩ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፤ እንዲሁም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን በመንበረ ጸባዖት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት ሥርዓተ ጸሎቱ ቀጥሏል፡፡
ከኪዳን ጸሎት በኋላ ሥርዓተ ቅዳሴው ቀጥሎ ፤ ከሥርዓተ ቅዳሴው ጋር በማያያዝ የቅዱስ ፓትርያርኩ ሥርዓተ ሢመት በአቃቤ መንበሩ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እየተመራ በማከናወን ቅዱስ ፓትርያርኩ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማገልገል ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፡፡ ከሥርዓተ ሢመቱ በኋላ ከአኀት ቤተ ክርስቲያናት መካከል የሕንድ፤ የግብጽ እንዲሁም የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናት በየተራ ጸሎት አድርሰዋል፡፡
abune mathias entronment
ሥርዓተ ቅዳሴው እንደተጠናቀቀ በአውደ ምሕረት ላይ የተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ተከናውነዋል፡፡ የአኀት ቤተ ክርስቲያናት እንዲሁም ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛው ፓትርያርክ ሆነው በመሾማቸው መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ  ለቤተ ክርስቲያኒቱና ለአገር እድገት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
ዝርዝሩን ይከታተሉን፡፡