abune paulos

ነሐሴ 17/2004 ዓ.ም. ቀጥታ ስርጫት ከመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ

abune paulos

 

ቀጣይ ያለውን መርሀ ግብር ለማቅረብ ከቦታ ጥበትና ከሰው መጨናነቅ የተነሣ ማስተላለፍ ስላልቻልን ከቀብር ስነ ሥርዓቱ በኋላ የመርሀ ግብሩን ሁኔታ በዝርዝርና በፎቶ ግራፍ የምናቀርብ ይሆናል፡

6:00 የኢትዮጵያ ሀይማኖቶች አንድነትን ጉባኤ በመወከል ሼህ አህመዲን የሀዘን መግለጫ እያስተላለፉ ነው፡፡
5:49 የኖርዌይ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የሀዘን መግለጫ መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡፡

5፡44 የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ፖፕ የሀዘን መግለጫ  መልዕክት በተወካያቸው  እየቀረበ ነው፡

5:38 የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተወካይ የሀዘን መግለጫ እያቀረቡ ናቸው፡

5፡32 የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ተወካይ መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡

ከኢፌዲሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ  መልዕክት በንግግራቸው ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፡-
•    ቤተ ክርስቲያኗን በዓለም መድረክ እንዳስተዋወቁ ፣
•    በሀገሪቷ የተከሰተውን የኤች. አይ.ቪ ኤድስ በሽታን እንደተከላከሉ
•    በሀገራችን ባሉ ሀይማኖቶች መካከል ሰላምና መግባባት እንዲኖር እንደሰሩ፣
•    የሰላም አምባሳደር በመሆን ከኢትዮጵያ አልፈው በዓለም መድረክ ከፍተኛ ሚና እንደተጫወቱ ገልጸዋል፡፡
•    ተተኪ የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎችም የቅዱስነታቸውን አርአያ ተከትለው መልካም አስተዳደርን በቤተ ክርስቲኗ እንዲያሰፍኑ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

5፡26 የኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበር አቡነ ጳኩሚስ መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡

5፡22 የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ የሀዘን መግለጫ መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡

5፡14 የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት ህብረቱን በመግለጽ የሀዘን መግለጫ እያስተላለፉ ነው፡፡5፡14 የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት ህብረቱን በመግለጽ የሀዘን መግለጫ እያስተላለፉ ነው፡፡

5፡09 የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት መልዕክት በተወካዩ አቶ አሰፋ ቀሲቶ አማካኝነት በመነበብ ላይ ነው፡

5፡05 የኢፌዲሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሀዘን መግለጫ መልዕክት በማስተላለፍ ላይ ናቸው፡፡

4፡54 ከአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ዜማ እያቀረቡ ናቸው፡፡

4:30 ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት የተውጣጡ ካህናት ያሬዳዊ ዜማ እያቀረቡ ናቸው፡፡

4፡54 ከአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ዜማ እያቀረቡ ናቸው፡፡

4፡22 የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክስቲያን ልዑካን ጸሎት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡

በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት በተለዩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የተመራው የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ጸሎት ማድረጉ ይታወሳል፡፡

በአንድ እኅት ቤተ ክርስቲያን የዚህ ዓይነት ሐዘን በሚደርስበት ጊዜ በሌሎች አኃት አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች ጸሎት መደረጉ የተለመደ ሥርዓት ነው፡፡

4:13 የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ልዑካን ጸሎት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡

4፡04 የአርመንያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ልዑካን ጸሎት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡

3፡55 በኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበር መሪነት ከቤተ ክርስቲያኗ የመጡ ካህናት ጸሎት እያደረጉ ነው፡፡

በዕለቱ እየጣለ ባለው ዝናብ የተነሣ መርሀ  ግብሩ እየተከናወነ ያለው በዐውደ ምሕረቱ ላይ በተጣሉ ድንኳኖች ሥር ነው፡፡

3፡35 መርሐ ግበሩ በጸሎተ ወንጌል እየተከፈተ ነው፡፡

3፡30 በዐውደ ምሕረቱ ክቡራን የመንግሥት ተወካዮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የልዩ ልዩ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ የአድባራትና ገዳማት አለቆች፣ ካህናት ፣ መዘምራንና ምዕመናን ታድመዋል፡፡

3፡20 ጸሎተ ቅዳሴውና ቀኖና የሚያዝዘው ጸሎት ሁሉ ተፈጸሞ በአሁኑ ሰዓት አስከሬኑ ወደ ዐውደ ምሕረቱ ወጥቷል፡፡

Normal 0 false false false EN-US X-NONE AR-SA

4:30 ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት የተውጣጡ ካህናት ያሬዳዊ ዜማ እያቀረቡ ናቸው፡፡

4፡54 ከአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ዜማ እያቀረቡ ናቸው፡፡

5፡05 የኢፌዲሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሀዘን መግለጫ መልዕክት በማስተላለፍ ላይ ናቸው፡፡