abune paulos funeral1

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

“ከመቃብር ላይ ሆነን የምንናገረው ስለ ትንሣኤ እሙታን ነው” ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዐቃቢ መንበረ ፓትርያርክ

ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ

abune paulos funeral1 ብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝደንት፣ የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከአኀት አብያተ ክርስቲያናትና ከሌሎችም የተወከሉ የእምነት አባቶች በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡

Abune Paulos FuneralAbune Paulos Funeral0Abune Paulos Funeral

Abune Paulos Funeral15

Abune Paulos Funeral2Abune Paulos Funeral4 Abune Paulos Funeral9

Abune Paulos Funeral5Abune Paulos Funeral00Abune Paulos Funeral6

Abune Paulos Funeral10Abune Paulos Funeral11Abune Paulos Funeral13Abune Paulos Funeral14

Abune Paulos Funeral7Abune Paulos Funeral8

የቅዱስነታቸው አስክሬን ትናንት ረቡዕ (ነሐሴ 16 ቀን 2004ዓ.ም) ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ በካህናት ፣በሰንበት ትምህርት ቤቶች ዘማሪያንና በምእመናን ታጅቦ ከመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ከተወሰደ በኋላ በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ጸሎተ ፍትሐትና ማኅሌት ሲደርስ አድሯል፡፡ ዛሬ ንጋት ላይ ጸሎተ ቅዳሴው ከተከናወነ በኋላ ከግብፅ፣ከሶርያ፣ ከሕንድና ከአርመን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አኀት አብያተ ክርስቲያናት የተወከሉ አባቶች በየቋንቋቸው ጸሎት አድርሰዋል፡፡

በሥርዓተ ቀብሩ ላይ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ፕሬዝደንት  የተከበሩ አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የላኩትን የሐዘን መግለጫ በተወካያቸው አቶAbune Paulos Funeral14 አሰፋ ከሲቶ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን፣ በተመሳሳይ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ጊዚያዊ ጠቅላይ ሚንስትርና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር  አቶ ሃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ እንዲሁም የአዲስ አባባ ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ በየተራ በቅዱስነታቸው ዕረፍት ምክንያት የተሰማቸውን ልባዊ ሐዘን ገልጠዋል፡፡

Abune Paulos Funeral Liturgyሥርዓተ ቀብሩን በመምራት ያስፈጸሙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበርና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ባስተላለፉት ቃለ ምእዳንና ጸሎተ ቡራኬ፡-“…እኛ ከዚህ መቃብር ላይ ሆነን የምንናገረው ስለ መቃብር አይደለም፤ ስለ ትንሣኤ ሙታን ነው እንጂ፤ ” ብለዋል፡፡ ብፁዕነታቸው በዚሁ መልእክታቸው የቅዱስ ፓትርያርኩን ቅድስና አውስተው ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡ የሕይወት ታሪካቸውን ይህን በመጫን ያንብቡ