የአዲስ ዘመን ቆይታችን

ግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ጸበል ጸዲቅ /ክፍል ስድስት/
የማኅበሩ ጋዜጠኞች ቡድን ወደ ሰሜን ጎንደር፤ ደቡብ ጎንደር፤ ምእራብ ጎጃምና አዊ ዞን የሚገኙ ቅዱሳት መካናትንና የሀገረ ስብከቶቹን የሥራ እንቅስቃሴ ለመዘገብ ከሚያዚያ 3 -20 ቀን 2005 ዓ.ም. ያደረገውን ጉዞ አጠናቅቆ ተመልሷል፡፡ በዚህም መሠረት በጉዟችን ያሰባሰብናቸውን መረጃዎች አቀናጅተን በድረ ገጻችን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡

በጉዟችን ወቅት እየዳሰስናቸው የነበሩትን መረጃዎች “ጸበል ጸዲቅ” በሚል ርዕስ ክፍል አምስት ድረስ ማቃመሳችን ይታወቃል፡፡ ከክፍል ስድስት ጀምሮ ያሉትን ደግሞ እነሆ፡-

የጋዜጠኞቹ ቡድን ከዚህ በፊት ብዙም ትኩረት ያልተሰጣቸውና በዝዋይ ሐይቅ  የሚገኙትን የቅዱሳን አበው የሃይማኖት ፍሬ የሆኑት ገዳማትን ቃኝተን ፤ የሰሜን ጎንደር ቆይታችንን በማጠናቀቅ ወደ ደቡብ ጎንደር በማቅናት ሥራችንን ከአዲስ ዘመን ለመጀመር ወስነናል፡፡

አዲስ ዘመን ከተማ የደረስነው በምሽት ስለነበር የወረዳ ማእከሉ ወንድሞችና እህቶች ተቀብለውን፤ ማረፊያ አዘጋጅተው፤ እግራችንን አጥበው፤ ምግብ እያቀረቡልን በጥሩ መስተንግዶ ተንከባክበውናል፡፡

ጉዟችንን ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ በየቀኑ ምሽት ከማረፋችን በፊት ውሏችንን በተመለከተ እያንዳንዱ ጋዜጠኛ ለቡድኑ የቃል ሪፖርት ያቀርባል፡፡ ከሪፖርቱም በመነሳት ውይይት በማድረግ ስህተቶች ካሉም ወደፊት በሚሰራው ሥራ ላይ እንዲስተካከል በመመካከር በቀጣዩ ቀን የሚዘገቡ ሥራዎችን እንከፋፈላለን፡፡

በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ውስጥ ለመሰራት ከታቀዱት ቤተ ክርስቲያናትና ገዳማት መካከል ዜና ማርያም፤ ዋሻ አቡነ እንድርያስ፤ ወይን ዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤ ጣራ ገዳም፤ ሊቦ ቅዱስ ጊዮርጊስንና ሐና ማርያምን ለማዳረስ ቡድኑ ጥረት አድርጓል፡፡

ዜና ማርያም ለመዘገብ ዲያቆን ቴዎድሮስ ኃይሉና መንገዱን ከሚመራው የአዲስ ዘመን ወረዳ ማእከል ወንድም ጋር ለአራት ሰዓታት የእግር መንገድ ቢጓዙም ሳይሳካላቸው ተመልሰዋል፡፡ የጉዟቸውን ሂደትና ያጋጠማቸውን ውጣ ውረድ እንዲህ ነበር የገለጸው፡-

ዜና ማርያም የትውልድ አገሯ ጎጃም ሲሆን በአገራችን ጽላቷ በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በአዲስ ዘመን ከተማ አቅራቢያ ብቻ ይገኛል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኗ ለመድረስ የፈለገ ሰው ከአዲስ ዘመን ከተማ ከሦስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት የእግር ጉዞ ማድረግ ግድ ይለዋል፡፡

ገዳሟ ተራራ ጫፍ ላይ የተመሠረተች በመሆኗ ገና ከአዲስ ዘመን ከተማ እግራችን መውጣት ሳይጀምር ነው በርቀት የተመለከትናት፡፡ በመንገድ ላይም ጥንታውያን የሆኑ ሁለት አብተ ክርስቲያናትን የደሪጣ መድኀኔዓለምን ደብር እና ደሪጣ ማርያምን ተሳለምን፡፡

እነዚህን አብያተ ክርስቲያናትን ተሳልመን ሜዳማ መንገዱን ጨርሰን ቀጥ ብሎ ከሩቅ ቆሞ ይጠብቀን ወደ ነበረው ተራራ አመራን፡፡ ተራራውን በእጅና በእግር ከመቧጠጥ ባልተናነሰ ሁኔታና ዐሥር ጊዜ እያረፍን ወጣነው፡፡

ወደ ገዳሟ ስንቀርብ መንገድ የሚመራው ዲ/ን ኀይለሚካኤል ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ እያመለከተ “እዚህ ተራራ ሥር የዜና ማርያም ጸበል አለ” አለን፡፡ አያይዞም “ጸበሉ በፈዋሽነቱ ስለሚታወቅ በቅርብ ርቀት የሚያውቁት ሁሉ እየመጡ ከተለያዩ ደዌያት እየተፈወሱ ይገኛሉ” በማለት ምስክርነቱን ሰጠን፡፡

እኛም የጸበሉን ቦታ አልፈን ተራራ ለተራራ እየተጓዝን ከገዳሟ መግቢያ በር ደረስንና “በሰላም ከደጅሽ ያደረስሽን” በማለት ጸሎት አደረግን፤ በዙሪያችን ባሉ ድንጋዮች ላይ ቁጭ ስንል ገዳሟ ተራራ ጫፍ ላይ ያለች እንደመሆኗ መጠን ዙሪያ ገባውን ቁልጭ አድርጋ አሳየችን፡፡

ከገዳሙ አባቶች አንድ አባት አገኘንና የሚበላውንና የሚጠጣውን ቀምሰን፤ ከሀገረ ስብከት የተጻፈልንን ደብዳቤም አሳየናቸው፤ የመጣንበትን ዓላማም አወጋናቸው፡፡ እኒህ አባት ደብዳቤውን ደጋግመው አነበቡት፡፡ አብራቸው የነበረች አንዲት እኅትም በርቀት አሻግራ ደብዳቤውን ከጥግ እስከ ጥግ አነበበችውና “እኔ የሚገርመኝ” በማለት ንግግሯን ጀመረች “እኔ የሚገርመኝ ለምንድነው ይህችን ገዳም ሁሉ የሚፈልጋት? ገድሏን እንመልከተው? የሚሉት” በማለት ተናደደች፡፡ እኛም ቅርሶችን ለመጠበቅ መንፈሳዊ ቅንዓት ሊሆን ይችላል በማለት የመገናኛ ብዙኀንን ጥቅም ለማስረዳት ሞክረን ደብዳቤውን ወደ ያዙት አባት ፊታችንን ዘወር አደረግን፡፡ እኒህም አባት “ልጆቼ እዚህ ድረስ በመምጣት ይህችን ታላቅ ገዳም ለማስተዋወቅ መሞከራችሁ የሚያስመሰግናችሁ ነው፤ ነገር ግን ዜና ማርያም እንዲህ ዓይነት ነገር አትወድም፡፡ ከዚህ በፊትም የገዳሟን ታሪክ ለመዘገብ የመጡ ሰዎች ነበሩ፡፡ ግማሾቹ ዐይናቸው ታውሮ ወደ ገዳሙ መግባት ሲያቅታቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ ያለእርሷ ፈቃድ ታሪኳን ዘግበው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ በመንገድ ላይ በመኪና አደጋ ዐረፉ” አሉን፡፡ አያይዘውም “ባህታውያን በየዓመቱ ወደዚህች ቦታ እየመጡ ታሪኳን ለማንም አትንገሩ ብለው አውግዘውናል” በማለት ለሰሚ ግራ የሆነ ንግግር አሰሙን፡፡ እሳቸው እኔ ብቻ የከለከልኳችሁ አይምሰል በሚመስል ሁኔታ “ኑ ወደ አስተዳዳሪው ቤት ልውሰዳችሁና እርሳቸውም የሚሉትን ስሙ” አሉን፡፡

የአስተዳዳሪው ቤት ለመድረስ ተጨማሪ ከዐሥራ አምስት ደቂቃ ያላነሰ መንገድ መሄድ ግድ ሆነብን፡፡ አስተዳዳሪው ይገኙበታል ወደተባለው ቤት ተጉዘን ሳንደርስ በመንገድ “እናንተ እዚህ ጋር ዐረፍ በሉና አስተዳዳሪው ካሉ ጠይቄ ልምጣ” ብለው ይዘውን የመጡት አባት በመንገድ ትተውን ሄዱ፡፡

ብዙ ታሪክ እንዘግባለን፤ ለምዕመናንም እናስተዋውቃለን ብለን ተስፋ ጥለን የመጣንበትን ነገር አንድም ሥራ ሳንሠራ እየመሸ በመሆኑ ተጨነቅን፡፡ እኚህን አባት በዐይናችን ስንከተላቸው በአካባቢው ከሚገኙ የሣር ጎጆዎች ወደ አንዲ ዘለቁ፤ ብዙም ሳይቆዩ ፈጥነው ተመለሱና “ዛሬ ዕድለኞች አይደላችሁም አስተዳዳሪው ስብሰባ ሄደዋል” አሉን፡፡ እኛም “ታዲያ ምን ይሻላል? እርሳቸው የሚፈቅዱልን ከሆነ እዚሁ እናንተ ዘንድ አድረን ጠዋት እናነጋግራቸው” አልናቸው፡፡ እርሳቸው ግን “እዚህ ብታድሩም አሁን ከነገርኳችሁ ውጪ የምትሰሙት ነገር የለም፤ ፈቃድ ለማግኘት የሚቻለው ከአስተዳዳሪው ወይም ከሰበካው ሳይሆን ሕዝቡ ሲፈቅድ ነው፡፡ የሕዝቡን ፈቃድ ለማግኘት ደግሞ ጊዜ ያስፈልጋል፤ ሳይመሽባችሁ ሂዱ” ብለው መንገድ አመላክተው ሸኙን፡፡

እኛም ዝናብና ጨለማ ሳያገኘን አዲስ ዘመን ለመግባት የደከመ ጉልበታችንን ማንቀሳቀስ ጀመርን፡፡ ነገር ግን እግራችን በፈለግነው ፍጥነት መጓዝ ባለመቻሉ ሊወርድ ካለው በረዶና ከሚያስፈራው ጨለማ ማምለጥ ሳንችል ቀረን፡፡ 

እነ ዲያቆን ቴዎድሮስ ኀይሉ የዜና ማርያምን ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ለመዘገብ ሄደው ያጋጠማቸውን ነበር ያወጉን፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና የቅዲሳን አባቶቻችን እንዲሁም እናቶቻችን ታሪክና ገድል እንዳይታወቅ በስመ ውግዘት አፍኖ ማስቀረቱ ማንን ነው የሚጠቅመው? ማውገዝ የሚችለውስ ማነው? የውግዘት ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? ምላሽ የሚፈልጉ ጥያቄዎች ናቸው፡፡

ወደ ሊቦ ቅዱስ ጊዮርጊስ የተጓዘው ዲያቆን ታደለ ሲሳይና መንገዱን ከሚመራው ወንድም ጋር ከአምስት ሰዓታት በላይ የእግር ጉዞ ወስዶባቸው ነው ቦታው የደረሱት፡፡ በእለቱ መመለስ ባለመቻላቸው አዳራቸውን እዚያው አድርገው በማግስቱ ሲመለሱ መንገድ ተሳስተው ተንከራትተው ነው አዲስ ዘመን የገቡት፡፡ ማካካሻ ይሆናቸው ዘንድ ግን የሚፈለገውን መረጃ ይዘው መምጣታቸው አስደሳች ነበር፡፡

ይቆየን


1024×768

የአዲስ ዘመን ቆይታችን

ጸበል ጸዲቅ /ክፍል ስድስት/

ግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የማኅበሩ ጋዜጠኞች ቡድን ወደ ሰሜን ጎንደር፤ ደቡብ ጎንደር፤ ምእራብ ጎጃምና አዊ ዞን የሚገኙ ቅዱሳት መካናትንና የሀገረ ስብከቶቹን የሥራ እንቅስቃሴ ለመዘገብ ከሚያዚያ 3 -20 ቀን 2005 ዓ.ም. ያደረገውን ጉዞ አጠናቅቆ ተመልሷል፡፡ በዚህም መሠረት በጉዟችን ያሰባሰብናቸውን መረጃዎች አቀናጅተን በድረ ገጻችን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡

በጉዟችን ወቅት እየዳሰስናቸው የነበሩትን መረጃዎች “ጸበል ጸዲቅ” በሚል ርዕስ ክፍል አምስት ድረስ ማቃመሳችን ይታወቃል፡፡ ከክፍል ስድስት ጀምሮ ያሉትን ደግሞ እነሆ፡-

የጋዜጠኞቹ ቡድን ከዚህ በፊት ብዙም ትኩረት ያልተሰጣቸውና በዝዋይ ሐይቅ  የሚገኙትን የቅዱሳን አበው የሃይማኖት ፍሬ የሆኑት ገዳማትን ቃኝተን ፤ የሰሜን ጎንደር ቆይታችንን በማጠናቀቅ ወደ ደቡብ ጎንደር በማቅናት ሥራችንን ከአዲስ ዘመን ለመጀመር ወስነናል፡፡

አዲስ ዘመን ከተማ የደረስነው በምሽት ስለነበር የወረዳ ማእከሉ ወንድሞችና እህቶች ተቀብለውን፤ ማረፊያ አዘጋጅተው፤ እግራችንን አጥበው፤ ምግብ እያቀረቡልን በጥሩ መስተንግዶ ተንከባክበውናል፡፡

ጉዟችንን ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ በየቀኑ ምሽት ከማረፋችን በፊት ውሏችንን በተመለከተ እያንዳንዱ ጋዜጠኛ ለቡድኑ የቃል ሪፖርት ያቀርባል፡፡ ከሪፖርቱም በመነሳት ውይይት በማድረግ ስህተቶች ካሉም ወደፊት በሚሰራው ሥራ ላይ እንዲስተካከል በመመካከር በቀጣዩ ቀን የሚዘገቡ ሥራዎችን እንከፋፈላለን፡፡

በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ውስጥ ለመሰራት ከታቀዱት ቤተ ክርስቲያናትና ገዳማት መካከል ዜና ማርያም፤ ዋሻ አቡነ እንድርያስ፤ ወይን ዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤ ጣራ ገዳም፤ ሊቦ ቅዱስ ጊዮርጊስንና ሐና ማርያምን ለማዳረስ ቡድኑ ጥረት አድርጓል፡፡

ዜና ማርያም ለመዘገብ ዲያቆን ቴዎድሮስ ኃይሉና መንገዱን ከሚመራው የአዲስ ዘመን ወረዳ ማእከል ወንድም ጋር ለአራት ሰዓታት የእግር መንገድ ቢጓዙም ሳይሳካላቸው ተመልሰዋል፡፡ የጉዟቸውን ሂደትና ያጋጠማቸውን ውጣ ውረድ እንዲህ ነበር የገለጸው፡-

ዜና ማርያም የትውልድ አገሯ ጎጃም ሲሆን በአገራችን ጽላቷ በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በአዲስ ዘመን ከተማ አቅራቢያ ብቻ ይገኛል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኗ ለመድረስ የፈለገ ሰው ከአዲስ ዘመን ከተማ ከሦስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት የእግር ጉዞ ማድረግ ግድ ይለዋል፡፡

ገዳሟ ተራራ ጫፍ ላይ የተመሠረተች በመሆኗ ገና ከአዲስ ዘመን ከተማ እግራችን መውጣት ሳይጀምር ነው በርቀት የተመለከትናት፡፡ በመንገድ ላይም ጥንታውያን የሆኑ ሁለት አብተ ክርስቲያናትን የደሪጣ መድኀኔዓለምን ደብር እና ደሪጣ ማርያምን ተሳለምን፡፡

እነዚህን አብያተ ክርስቲያናትን ተሳልመን ሜዳማ መንገዱን ጨርሰን ቀጥ ብሎ ከሩቅ ቆሞ ይጠብቀን ወደ ነበረው ተራራ አመራን፡፡ ተራራውን በእጅና በእግር ከመቧጠጥ ባልተናነሰ ሁኔታና ዐሥር ጊዜ እያረፍን ወጣነው፡፡

ወደ ገዳሟ ስንቀርብ መንገድ የሚመራው ዲ/ን ኀይለሚካኤል ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ እያመለከተ “እዚህ ተራራ ሥር የዜና ማርያም ጸበል አለ” አለን፡፡ አያይዞም “ጸበሉ በፈዋሽነቱ ስለሚታወቅ በቅርብ ርቀት የሚያውቁት ሁሉ እየመጡ ከተለያዩ ደዌያት እየተፈወሱ ይገኛሉ” በማለት ምስክርነቱን ሰጠን፡፡

እኛም የጸበሉን ቦታ አልፈን ተራራ ለተራራ እየተጓዝን ከገዳሟ መግቢያ በር ደረስንና “በሰላም ከደጅሽ ያደረስሽን” በማለት ጸሎት አደረግን፤ በዙሪያችን ባሉ ድንጋዮች ላይ ቁጭ ስንል ገዳሟ ተራራ ጫፍ ላይ ያለች እንደመሆኗ መጠን ዙሪያ ገባውን ቁልጭ አድርጋ አሳየችን፡፡

ከገዳሙ አባቶች አንድ አባት አገኘንና የሚበላውንና የሚጠጣውን ቀምሰን፤ ከሀገረ ስብከት የተጻፈልንን ደብዳቤም አሳየናቸው፤ የመጣንበትን ዓላማም አወጋናቸው፡፡ እኒህ አባት ደብዳቤውን ደጋግመው አነበቡት፡፡ አብራቸው የነበረች አንዲት እኅትም በርቀት አሻግራ ደብዳቤውን ከጥግ እስከ ጥግ አነበበችውና “እኔ የሚገርመኝ” በማለት ንግግሯን ጀመረች “እኔ የሚገርመኝ ለምንድነው ይህችን ገዳም ሁሉ የሚፈልጋት? ገድሏን እንመልከተው? የሚሉት” በማለት ተናደደች፡፡ እኛም ቅርሶችን ለመጠበቅ መንፈሳዊ ቅንዓት ሊሆን ይችላል በማለት የመገናኛ ብዙኀንን ጥቅም ለማስረዳት ሞክረን ደብዳቤውን ወደ ያዙት አባት ፊታችንን ዘወር አደረግን፡፡ እኒህም አባት “ልጆቼ እዚህ ድረስ በመምጣት ይህችን ታላቅ ገዳም ለማስተዋወቅ መሞከራችሁ የሚያስመሰግናችሁ ነው፤ ነገር ግን ዜና ማርያም እንዲህ ዓይነት ነገር አትወድም፡፡ ከዚህ በፊትም የገዳሟን ታሪክ ለመዘገብ የመጡ ሰዎች ነበሩ፡፡ ግማሾቹ ዐይናቸው ታውሮ ወደ ገዳሙ መግባት ሲያቅታቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ ያለእርሷ ፈቃድ ታሪኳን ዘግበው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ በመንገድ ላይ በመኪና አደጋ ዐረፉ” አሉን፡፡ አያይዘውም “ባህታውያን በየዓመቱ ወደዚህች ቦታ እየመጡ ታሪኳን ለማንም አትንገሩ ብለው አውግዘውናል” በማለት ለሰሚ ግራ የሆነ ንግግር አሰሙን፡፡ እሳቸው እኔ ብቻ የከለከልኳችሁ አይምሰል በሚመስል ሁኔታ “ኑ ወደ አስተዳዳሪው ቤት ልውሰዳችሁና እርሳቸውም የሚሉትን ስሙ” አሉን፡፡

የአስተዳዳሪው ቤት ለመድረስ ተጨማሪ ከዐሥራ አምስት ደቂቃ ያላነሰ መንገድ መሄድ ግድ ሆነብን፡፡ አስተዳዳሪው ይገኙበታል ወደተባለው ቤት ተጉዘን ሳንደርስ በመንገድ “እናንተ እዚህ ጋር ዐረፍ በሉና አስተዳዳሪው ካሉ ጠይቄ ልምጣ” ብለው ይዘውን የመጡት አባት በመንገድ ትተውን ሄዱ፡፡

ብዙ ታሪክ እንዘግባለን፤ ለምዕመናንም እናስተዋውቃለን ብለን ተስፋ ጥለን የመጣንበትን ነገር አንድም ሥራ ሳንሠራ እየመሸ በመሆኑ ተጨነቅን፡፡ እኚህን አባት በዐይናችን ስንከተላቸው በአካባቢው ከሚገኙ የሣር ጎጆዎች ወደ አንዲ ዘለቁ፤ ብዙም ሳይቆዩ ፈጥነው ተመለሱና “ዛሬ ዕድለኞች አይደላችሁም አስተዳዳሪው ስብሰባ ሄደዋል” አሉን፡፡ እኛም “ታዲያ ምን ይሻላል? እርሳቸው የሚፈቅዱልን ከሆነ እዚሁ እናንተ ዘንድ አድረን ጠዋት እናነጋግራቸው” አልናቸው፡፡ እርሳቸው ግን “እዚህ ብታድሩም አሁን ከነገርኳችሁ ውጪ የምትሰሙት ነገር የለም፤ ፈቃድ ለማግኘት የሚቻለው ከአስተዳዳሪው ወይም ከሰበካው ሳይሆን ሕዝቡ ሲፈቅድ ነው፡፡ የሕዝቡን ፈቃድ ለማግኘት ደግሞ ጊዜ ያስፈልጋል፤ ሳይመሽባችሁ ሂዱ” ብለው መንገድ አመላክተው ሸኙን፡፡

እኛም ዝናብና ጨለማ ሳያገኘን አዲስ ዘመን ለመግባት የደከመ ጉልበታችንን ማንቀሳቀስ ጀመርን፡፡ ነገር ግን እግራችን በፈለግነው ፍጥነት መጓዝ ባለመቻሉ ሊወርድ ካለው በረዶና ከሚያስፈራው ጨለማ ማምለጥ ሳንችል ቀረን፡፡  

እነ ዲያቆን ቴዎድሮስ ኀይሉ የዜና ማርያምን ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ለመዘገብ ሄደው ያጋጠማቸውን ነበር ያወጉን፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና የቅዲሳን አባቶቻችን እንዲሁም እናቶቻችን ታሪክና ገድል እንዳይታወቅ በስመ ውግዘት አፍኖ ማስቀረቱ ማንን ነው የሚጠቅመው? ማውገዝ የሚችለውስ ማነው? የውግዘት ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? ምላሽ የሚፈልጉ ጥያቄዎች ናቸው፡፡

ወደ ሊቦ ቅዱስ ጊዮርጊስ የተጓዘው ዲያቆን ታደለ ሲሳይና መንገዱን ከሚመራው ወንድም ጋር ከአምስት ሰዓታት በላይ የእግር ጉዞ ወስዶባቸው ነው ቦታው የደረሱት፡፡ በእለቱ መመለስ ባለመቻላቸው አዳራቸውን እዚያው አድርገው በማግስቱ ሲመለሱ መንገድ ተሳስተው ተንከራትተው ነው አዲስ ዘመን የገቡት፡፡ ማካካሻ ይሆናቸው ዘንድ ግን የሚፈለገውን መረጃ ይዘው መምጣታቸው አስደሳች ነበር፡፡

ይቆየን

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና የቅዱሳን አባቶቻችን እንዲሁም እናቶቻችን ታሪክና ገድል እንዳይታወቅ በስመ ውግዘት አፍኖ ማስቀረቱ ማንን ነው የሚጠቅመው? ማውገዝ የሚችለውስ ማነው? የውግዘት ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? ምላሽ የሚፈልጉ ጥያቄዎች ናቸው፡፡

ወደ ዲቦ ቅዱስ ጊዮርጊስ የተጓዘው ዲያቆን ታደለ ሲሳይና መንገዱን ከሚመራው ወንድም ጋር ከአምስት ሰዓታት በላይ የእግር ጉዞ ወስዶባቸው ነው ቦታው የደረሱት፡፡ በእለቱ መመለስ ባለመቻላቸው አዳራቸውን እዚያው አድርገው በማግስቱ ሲመለሱ መንገድ ተሳስተው ተንከራትተው ነው አዲስ ዘመን የገቡት፡፡ ማካካሻ ይሆናቸው ዘንድ ግን የሚፈለገውን መረጃ ይዘው መምጣታቸው አስደሳች ነበር፡፡

እኔና የቴሌቪዥን ክፍል አዘጋጁ ቶማስ በየነ ከቪዲዮ ካሜራ ባለሙያው ሙሉጌታ ቢሆነኝ ጋር በሊቀ መንኮራኩራችን /ሾፌራችን/ ነብያት መንግስቴ አብራሪነት ወደ አቡነ እንድርያስ ዋሻና ወይን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዋሻ ገሰገስን፡፡ መኪና መንገዱን ትተን ጥቂት ወደ ቀኝ እንደታጠፍን ትልልቅ ድንጋዮች አጋጠሙን፡፡

ነብያት መኪናውን አቁሞ “እንዴት በዚህ መንገድ ሂድ ትሉኛላችሁ፤ ለመኪናው አስቡ እንጂ!” በማለት ወርዶ በኩርፊያ ድንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡

ያለን አማራጭ ለቪዲዮ ቀረጻ የሚያገለግሉንን መሳሪያዎች ከመኪናው ላይ አውርደን በመከፋፈል   ተሸክመን ጉዟችንን ቀጠልን፡፡ ከአርባ ደቂቃ የእግር ጉዞ በኋላ አቡነ እንድርያስ ዋሻ ደረስን፡፡

አቡነ እንድርያስ ገዳም/አቡነ እንድርያስ ዋሻ/፤-

የአቡነ እንድርያስ ገዳም ከአዲስ ዘመን ከተማ በስተሰሜን አቅጣጫ ከተራራ ሥር የሚገኝ የዋሻ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ በአካባቢው በተለምዶ እንድርያስ ዋሻ በመባል ይታወቃል፡፡

ገዳሙ አራት በሮች ሲኖሩት እያንዳንዳቸው ከአንድ  ወጥ እንጨት ተጠርበው የተሰሩ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ደረጃና የበሩ መቃን በጣና ደሴት ውስጥ ከሚገኙት ከደብረ ሲና ማርያም፤ ከደብረ ገሊላ ኢየሱስ አቡነ ዘካርያስ ገዳም፤ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም፤ . . . ጋር ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ገዳሙ ምንም ዓይነት እድሳት ያልተደረገለት ሲሆን ጥንታዊነቱን ጠብቆ የሚገኝ የዋሻ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡  

ቀሲስ ቢራራ በላቸው ይባላሉ፡፡ የገዳሙ አገልጋይና ቁልፍ ያዥ ናቸው፡፡ ስለ ገዳሙ ካጫወቱንና በገዳሙ ውስጥ ከሚገኘው ከአቡነ እንድርያስ ገድል ካገኘነው በጥቂቱ ላቅርብላችሁ፡፡

ቦታው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ899 ዓ.ዓ. በአፄ ባዚን ዘመነ መንግስት የተመሠረተና የአካባቢው ሰዎች በእንጨት ምስል ቀርጸው ጣኦት እያመለኩ ቆይተውበታል፡፡ ለ440 ዓመታትም የኦሪት መስዋዕት ሲሰዋበት የነበረ ሲሆን፤ የአካባቢው ነዋሪዎች ዋሻው ውስጥ የሚኖሩ ሁለት ባልና ሚስት  ዘንዶዎችን እርጎ እየመገቡ ያመልኳቸው እንደነበር በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው ገድለ አቡነ እንድርያስ ይገልጻል፡፡

በሩን ከፍተው ወደ ውስጥ ሲዘልቁ ሰፊውን ቅኔ ማኅሌት ያገኛሉ፤ ከፊት ለፊት ቅድስትና መቅደሱ፤ እንዲሁም በትልቁ የተሳሉ የአቡነ እንድርያስ ስእሎች ጎልተው ይታያሉ፡፡ በቤተ መቅደሱ ግራና ቀኝ ሰልፋና ደፈር በተባሉ ሰዎች በጥርብ ድንጋይ የተከለሉ ቦታዎች አሉ፡፡ /ሰልፋና ደፈር የዘንዶዎቹ ቀላቢዎች/ እንደነበሩ ገድለ አቡነ እንድርያስን በመጥቀስ አባቶች ይናገራሉ፡፡

ገዳሙ ከክርስቶስ ልደት በኋላም የአካባቢው ሕዝብ ዘንዶዎቹን በማምለክ የቆየ ሲሆን አቡነ እንድርያስ በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት በደቀመዛሙርትነት ተመርጠው ምድረ እንፍራንዝ /የአሁኑ ሊቦ ከምከም ወረዳ አካባቢ/ ሄደው ክርስትና እንዲያስተምሩ፤ ህዝቡንም እንዲያጠምቁ ተልከዋል፡፡

አቡነ እንድርያስ ተልእኳቸውን ለመፈጸም ወደ አካባቢው ሲመጡ ረድአቸውን አቡነ ቶማስን አስከትለው ስለነበር አካባቢውን እንዲቃኙና ለጸሎት የሚመች ቦታ እንዲፈልጉ ላኳቸው፡፡ ይህ ዋሻ በአቡነ እንድርያስ ረድእ በነበሩት በአቡነ ቶማስ አማካይነት የተገኘ ሲሆን ዘንዶዎቹን ሲመለከቱ በመፍራታቸው ቦታው እንደማይሆናቸውና የዘንዶዎቹን አስፈሪነት ለአቡነ እንድርያስ ይገልጹላቸዋል፡፡ አቡነ እንድርያስም “በእግዚአብሔር ኃይል እናሸንፋቸዋለን” በማለት መጥተው በመስቀላቸው በማማተብ በእግዚአብሔር ስም ይገስጻቸዋል፡፡ በዚህ ቅጽበት አቡነ እንድርያስ የያዙት መስቀል ከመሬት ወድቆ የቀኝ በኩል ክንፉ በመሰበሩ ወደ እግዚአብሔር ቢጸልዩ የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ እንደነበረ አድርጎ ሰጥቷቸዋል፡፡ ከዘንዶዎቹ አንዱ ከአካባቢው ማዶ ተምዘግዝጎ ግራርጌ ጉበያ ማርያም ከሚባል ቦታ ላይ ወድቋል፡፡ አንደኛው ግን እስከ ዛሬ ድረስ የደረሰበት ባይታወቅም ወደ ዋሻው ውስጠኛ ክፍል ገብቶ እንደቀረ ይነገራል፡፡

አቡነ እንድርያስ ገዳሙን አቅንተው የአካባቢው ምእመናንን ክርስትና በማስተማር ታላቅ ተድጋሎ የፈጸሙበት ቅዱስ ስፍራ ነው፡፡ ወደ ገዳሙ በተአምራት አብረዋቸው የመጡ አራት በግምት አንድ ሜትር ቁመት ያላቸውና ከ20 እስከ አሥራ አምስት ሣንቲ ሜትር ስፋት ያላቸው ድንጋዮች መካከል ሁለቱ በደወልነት አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ ሲደወሉ ወፍራምና ቀጭን ድምጽ ስለሚያወጡ የወንድና የሴት ደወሎች ይባላሉ፡፡ በአገልግሎት ወቅት ዋሻው ድምጽ እያስተጋባ ስለሚያስቸግር አቡነ እንድርያስ ገስጸውት እስከ ዛሬ ድረስ ዋሻው ምንም አይነት ድምጽ አያስተጋባም፡፡

በገዳሙ ውስጥ ዜና ማርያም የተባለችው ቅድስት እናት ለ25 ዓመታት በጸሎት ተወስና ቆይታበታለች፡፡ ከእንጨት ተፈልፍሎ በቁመቷ ልክ በተሰራ ገንዳ ውስጥ ገብታ የገንዳውን ግራና ቀኝ በደረቷ አቅጣጫ በመብሳት በጠፍር በማሰር ትጸልይ ነበር፡፡/ ዜና ማርያም ትጸልይበት የነበረው የእንጨት ገንዳ ዛሬም በገዳሙ ውስጥ ይገኛል፡፡/

በገዳሙ ውሰጥ በጥንቃቄ ጉድለት እየተበላሹ የሚገኙት ቅርሶች እንደ አልባሌ እቃዎች ተጥለዋል ማለት ይቻላል፡፡ ዘንዶው እርጎ ይጠጣበት የነበረው ገንዳ፤ የዜና ማርያም መጸለያ ገንዳ፤ በእንጨት የተሰራ የኦሪት መሰዊያ፤ የመስዋእተ በግዕ ስጋ ማስቀመጫ፤ የደሙ ማኖሪያ፡ አፄ ዘርዓያዕቆብ ለገዳሙ ከሰጧቸው 6 ነጋሪቶች መካከል ሁለቱ፤  ብዛት ያላቸው የሰው አጽሞች ይገኛሉ፡፡ ከአጽሞቹ መካከል አንዱ ሙሉ ለሙሉ ሳይፈርስ ከራስ ቅሉ እስከ እግር ጥፍሩ በዘመናዊ ሳጥን ተደርጎ ከላይ በመስታወት ታሽጎ ይታያል፡፡ የአጽሞቹን እድሜ መገመ,ት እንደማይቻልና ቀድሞም እንደነበሩ ቀሲስ ቢራራ በላቸው ይገልጻሉ፡፡

የአቡነ እንደርያስ የእጅ መስቀል በገዳሙ ውስጥ በቅርስነት ተጠብቆ ይኖር እንደነበር፤ ብዛት ያላቸው ምእመናን በመስቀሉ ታሽተው ከያዛቸው ደዌ ይድኑ እንደነበር ቀሲስ ቢራራ በላቸው የአይን ምስክር እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን በቅርቡ በአንድ ግለሰብ የአቡነ እንድርያስ መስቀል መዘረፉንና የግለሰቡ ማንነት ታውቆ ክስ ተመስርቶበት በቀጠሮ ላይ እንደሚገኝ የአቡነ እንድርያስን ዋሻ ቆይታችንን አጠናቀን ስንወጣ የገዳሙ አበምኔት የክሱን ሁኔታ ለመከታተል ከሔዱበት ሲመለሱ አግኝተናቸው ነግረውናል፡፡

ገዳሙ ለስርቆት የተጋለጠ በመሆኑ የገዳሙ ጥንታዊ መጻሕፍት ተሰብስበው በአንድ ታማኝ በሆነ ግለሰብ ቤት ውስጥ እንዲቀመጥ መደረጉንም ቅርሶቹን ለማየት በጠየቅንበት ወቅት ከተሰጠን ምላሽ ለማወቅ ችለናል፡፡ የብራና መጻሕፍት ገድለ ሰማእታት፤ ስንክሳር የአመት /2/፤ ጸሎተ እጣን፤ ግንዘትና . . . ሌሎችም ንዋያተ ቅዱሳት በዚሁ ታማኝ ነው በተባለው ሰው እጅ ላይ ይገኛሉ፡፡ በየአመቱም ቆጠራ እንደሚካሔድ በስፍራው ከነበሩት አባቶች ተገልጾልናል፡፡

የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሀብቶችና ቅርሶች እሰከ መቼ በሰዎች እጅ ይቆያሉ? በተለያዩ ምክንያቶች ቢሰወሩ ተጠያቂው ማነው? መፍትሔ ይሻልና ሀገረ ስብከቱም ሆነ ምእመናን ትኩረት ሊሰጡት ይገባል፡፡

ምእመናን ተጠምቀው ከተያዙበት ደዌ የሚፈወሱበት ጸበል ከገዳሙ በስተ ደቡብ ይገኛል፡፡ ጸበሉ በምንጭነት የሚፈልቅ ሲሆን ምንም አይነት ከለላ ስላልተደረገለት ለከብቶችና ለአራዊት የተጋለጠ ነው፡፡

የኢሱስ፤ የቅዱስ ሚካኤልና የአቡነ እንድርያስ ታቦታት፤ እንዱሁም የአቡነ እንድርያስ መቃብር በዚሁ ዋሻ ቤተ መቅደስ ውስጥ ይገኛሉ፡፡

አቡነ እንድርያስ ግንቦት 20 ቀን ወደ ገዳሙ እንደገቡና ጳጉሜ 3 ቀን እንዳረፉ ገድላቸው የሚገልጽ ሲሆን ዓመተ ምሕረቱን ግን አይናገርም፡፡ በዚህም መሠረት ግንቦት 20 ቀን በየዓመቱ በገዳሙ በዓላቸው ይከበራል፡፡

ገዳሙ ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ የሌለው ሲሆን አገልጋዮቹ የራሳቸውን የእርሻ መሬት እያረሱ በሚያገኙት ይተዳደራሉ፡፡

ተሰጣቸው መልስ ከስርዓተ ቤተ ክርስስቲያን ውጪ የሆነና በግለሰቦች በጎ ፈቃድ ላይ ብቻ የተመሰረተ ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ ታሪክ፤ የዜና ማርያም ታሪክና ገድል በምስል ወድምጽ ወይም በፎቶ ግራፍ መውሰድ መልከሉን፤እንዲሁም በባህታዊያንና በአንድ አባት መወገዙን ተነግሯቸዋል፡፡ ለማሳመን ያደረጉት ጥረትም ሳይሳካ ቀረ፡፡ ሳይሳካላቸው መቅረቱ ብቻ ሳይሆን ወደ አዲስ ዘመን እየተመለሱ በረዶ በቀላቀለ ዝናብ መመታታቸው ደግሞ የሚያበሳጭ ነበር፡፡

ወይን ዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፡-

 

 

  

Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE