ጠቅላይ ቤተ ክህነት ደብሩ በ‹‹አጥማቂው›› ላይ የጣለውን እገዳ አጸና

በምሥራቅ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ ‹‹ሲያጠምቅ›› በነበረው ግለሰብ ላይ ያሳለፈውን የእግድ ውሳኔ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አጸናው፡፡ ከደብሩ ሰበካ ጉባኤ ያገኘውን የእግድ ደብዳቤ መሠረት በማድረግ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በቁጥር 9474/756/2005 በቀን 08/09/05 ያወጣው ደብዳቤ ‹‹መ/ር ግርማ ወንድሙ ሰባኬ ወንጌልና አጥማቂ ነኝ፤ የማዳን ፈውስ አለኝ በማለት በሕገ ወጥ መንገድ እስከ አሁን ድረስ በደብሩ እያጠመቀ›› እንደሚገኝ ይገልጻል፡፡

memher girma
በማከልም ቅዱስ ሲኖዶስ በሕገ ወጥ መንገድ የማዳን ፈውስ አለኝ በማለት በየደብሩ ቅጥር ግቢ በማሰባሰብ የሚያጠምቁትን በተመለከተ ያሳለፈውን የእግድ ውሳኔ በመጥቀስ፤ ‹‹መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እሰጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚፈጽሙት የማጥመቅ ሥርዓትና የወንጌል አገልግሎት ሕገ ወጥ መኾኑን›› በአጽንዖት በመግለጽ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት በግለሰቡ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዳጸናው ይገልጻል፡፡ በተጨማሪም ከእግዱ ጋር በተያያዘ ሕዝበ ክርስቲያኑ የፀጥታ ችግር እንዳይገጥመው የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ጥብቅ ክትትል በማድረግ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርግ አሳስቧል፡፡ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ለውሳኔው ተግባራዊነት አስፈላጊ ትብብር እንዲያደርጉ ለሚመለከታቸው የመንግሥት የፀጥታ አካላት ጥሪ አድርጓል፡፡ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ እና የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት እግዱን ያስተላለፈበት ደብዳቤዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

 betekihent girma